#ችሎት
" ንብረታችሁ ሊወረስ ነው " በማለት ባለሃብቱን አስፈራርተው በቼክ ገንዘብ ሲቀበሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ 4 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ተጠርጣሪዎቹ በብሔራዊ መረጃ ደህንነትና በፌደራል ፖሊስ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበትና በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የፋይናንስ ደህንነት ሰራተኞች ነን " በማለት አንድን ባለሃብት አስፈራርተው 5 ሚሊየን ብር ጉቦ ተደራድረው የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ተብሏል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ መዝገቦች ፍ/ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ፦
1ኛ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በሞጆ ደረቅ ወደብ የጥበቃ ኃላፊ ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ፤
2ኛ በግል ስራ የሚተዳደሩት ተስፋ ሀታኡ ገምቴሳ፣
3ኛ ጁዋር አወል ጀማል
4ኛ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የአይቲ ባለሙያ ረ/ኢ/ር ኩሉሌ ጉዮ ቦሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበት፣ በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበትና በጋዜጣ ባልታወጀበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " ደዘርት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር " ለተባለው ድርጅት ባለቤት አቶ ቢኒያም ሀደር እና ወኪላቸው ስራ አስኪያጅ መሐመድ እስማኤል አሊ ለተባሉት ግለሰቦች ስልካቸው ላይ ይደውላሉ።
ጥር 05 ቀን 2017 ጀምሮ ደግሞ በተለያዩ ቀናት ባለሃብቶቹን በአካል በማግኘት " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የመረጃ ደህንነት ሠራተኞች ነን " በማለት ይተዋወቃሉ።
" በአዲሱ ንብረት ማስመለስ አዋጅ መሰረት በንብረታችሁ ላይ እና የባንክ የሂሳብ እንቅስቃሴዎች ላይ ምርመራ ተደርጎ ንብረታችሁ ይወረሳል፤ የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ እናግዳለን " በማለት ሲያስፈራሩ እንደነበረ በጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ላይ ተብራርቷል።
በተለይ መንግስት ሃብታቸውን እንዳይወርስባቸው እንደሚያደርጉ በመግለጽ ለዚህ ማስፈጸሚያነት የሚውል 5 ሚሊየን ብር በመደራደር በቅድሚያ 20 ሺህ ብር በባንክ ሂሳብ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል አኑዋር ምግብ ቤት ውስጥ አንድ ሚሊየን ብር የተዘጋጀ ቼክ ከደርጅቱ ወኪል ከሆነው ከአቶ ማሐመድ እስማኤል አሊ እጅ ሲቀበሉ በክትትል ላይ በነበሩ ጸጥታ ኃይሎች መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ መርማሪ አሳውቋል።
መርማሪ ፖሊስ በዚህ መልኩ ተጠርጣሪዎቹ የሙስና ወንጀል የምርመራ ማጣሪያ ስራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከል ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ በሚመለከት የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ አስታውቋል።
በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ህግ በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ የምርመራ መዝገቡን ከዐቃቤ ህግ መረከቡን ጠቅሷል።
ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዘገቡን ተመልክቶ በተገቢው ሁኔታ ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጨማሪም ዐቃቤ ህግ በወንጀል ድርጊት ሊገኝ ከታሰበው የገንዘብ መጠን ወይም የደረሰው ጉዳት አንጻር ሲታይ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣና ዋስትና የሚያስከለክል መሆኑን ጠቅሶ ፤ የተጠርጣሪው ዋስትናው ታልፎ ክስ እስኪመሰረት ባሉበት በእስር እንዲቆዩ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ተጠርጣሪው የዐቃቤ ህግ ክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም ዋስትና እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የተጠርጣሪውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ህግ የዘጠኝ ቀናት ክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።
መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
@tikvahethiopia
" ንብረታችሁ ሊወረስ ነው " በማለት ባለሃብቱን አስፈራርተው በቼክ ገንዘብ ሲቀበሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ 4 ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ተጠርጣሪዎቹ በብሔራዊ መረጃ ደህንነትና በፌደራል ፖሊስ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበትና በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የፋይናንስ ደህንነት ሰራተኞች ነን " በማለት አንድን ባለሃብት አስፈራርተው 5 ሚሊየን ብር ጉቦ ተደራድረው የ1 ሚሊየን ብር ቼክ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ተብሏል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ መዝገቦች ፍ/ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ፦
1ኛ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በሞጆ ደረቅ ወደብ የጥበቃ ኃላፊ ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ፤
2ኛ በግል ስራ የሚተዳደሩት ተስፋ ሀታኡ ገምቴሳ፣
3ኛ ጁዋር አወል ጀማል
4ኛ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የአይቲ ባለሙያ ረ/ኢ/ር ኩሉሌ ጉዮ ቦሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው።
አዲሱ የንብረት ውርስ አዋጅ ወደ ስራ ባልገባበት፣ በፖሊስ ምርመራ ባልተጀመረበትና በጋዜጣ ባልታወጀበት ሁኔታ ላይ ተጠርጣሪዎቹ " ደዘርት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር " ለተባለው ድርጅት ባለቤት አቶ ቢኒያም ሀደር እና ወኪላቸው ስራ አስኪያጅ መሐመድ እስማኤል አሊ ለተባሉት ግለሰቦች ስልካቸው ላይ ይደውላሉ።
ጥር 05 ቀን 2017 ጀምሮ ደግሞ በተለያዩ ቀናት ባለሃብቶቹን በአካል በማግኘት " የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የመረጃ ደህንነት ሠራተኞች ነን " በማለት ይተዋወቃሉ።
" በአዲሱ ንብረት ማስመለስ አዋጅ መሰረት በንብረታችሁ ላይ እና የባንክ የሂሳብ እንቅስቃሴዎች ላይ ምርመራ ተደርጎ ንብረታችሁ ይወረሳል፤ የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ እናግዳለን " በማለት ሲያስፈራሩ እንደነበረ በጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ላይ ተብራርቷል።
በተለይ መንግስት ሃብታቸውን እንዳይወርስባቸው እንደሚያደርጉ በመግለጽ ለዚህ ማስፈጸሚያነት የሚውል 5 ሚሊየን ብር በመደራደር በቅድሚያ 20 ሺህ ብር በባንክ ሂሳብ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል አኑዋር ምግብ ቤት ውስጥ አንድ ሚሊየን ብር የተዘጋጀ ቼክ ከደርጅቱ ወኪል ከሆነው ከአቶ ማሐመድ እስማኤል አሊ እጅ ሲቀበሉ በክትትል ላይ በነበሩ ጸጥታ ኃይሎች መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ መርማሪ አሳውቋል።
መርማሪ ፖሊስ በዚህ መልኩ ተጠርጣሪዎቹ የሙስና ወንጀል የምርመራ ማጣሪያ ስራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከል ኢኒስፔክተር ሰለሞን ካሳ በሚመለከት የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ማስረከቡን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ፖሊስ አስታውቋል።
በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ህግ በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ የምርመራ መዝገቡን ከዐቃቤ ህግ መረከቡን ጠቅሷል።
ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዘገቡን ተመልክቶ በተገቢው ሁኔታ ክስ ለመመስረት እንዲያስችለው የ15 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጨማሪም ዐቃቤ ህግ በወንጀል ድርጊት ሊገኝ ከታሰበው የገንዘብ መጠን ወይም የደረሰው ጉዳት አንጻር ሲታይ ከ10 ዓመት በላይ የሚያስቀጣና ዋስትና የሚያስከለክል መሆኑን ጠቅሶ ፤ የተጠርጣሪው ዋስትናው ታልፎ ክስ እስኪመሰረት ባሉበት በእስር እንዲቆዩ እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ተጠርጣሪው የዐቃቤ ህግ ክስ መመስረቻ ጥያቄን በመቃወም ዋስትና እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የተጠርጣሪውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ህግ የዘጠኝ ቀናት ክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል።
መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።
@tikvahethiopia
👏319❤116😭35😡20🙏19🤔16😱12🥰9🕊7😢6
#ችሎት
⚫️ “ እኔን አጅባችሁ ውሰዱኝና ቤቱን ላሳያችሁ ” - አቶ ክርስቲያን ታደለ
🔴 “ ከአሁን ቀደምም በስም ማጥፋት ወንጀል ፍርድ ቤት ከስሸው ተቀቷል። ፖሊስ ቋሚ አድራሻ ቢኖረውም በተደጋጋሚ ሄዶ እያየ ሰላምታ እየሰጠው ነው የሚመለሰው ” - አቶ ዮሐንስ ቧያለው
የእነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌውን ጉዳይ የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የመንግስት አክቲቪስት” ሲሉ የጠሯቸውና “እነ ክርስቲያን ወንጀለኛ ናቸው” ያሉትን ግለሰብ ፌደራል ፓሊስ ማግኘት እንዳልቻለ ለፍርድ ቤት መግለጹን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
በዚህም፣ አቶ ስዩም ተሾመ የተባሉት ግለሰብ በቻናላቸው እነ አቶ ዮሐንስን ወንጀለኞች እንደሆኑ በመናገራቸው፣ እነ አቶ ዮሐንስም ክሰዋቸው ስለነበር ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ታዞ የነበረ ቢሆንም፣ ፌደራል ፓሊስ አቶ ስዩም ተሾመን ማግኘት አለመቻሉን ለፍርድ ቤት መግለጹን ነው ያስረዱት።
የእነ አቶ ዮሐንስ እና አቶ ክርስቲያን የቅርብ ሰዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ አቶ ዮሃንስ ቧያሌው እና ክርስቲያን ታደለ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ተከሰው ጉዳያቸው በመታዬት እያለ አቶ ስዩም ተሾመ መጋቢት 11/2017 ዓ/ም ባስተላለፉት ፕሮግራም ከተከሰሱበት ጉዳይ ጋር በተያያዘ ‘የአማራን ወጣት አስፈጅተዋል፣ ድሽቃ መሣሪያ መግዣ ጠይቀዋል’ ብለው እንደነበር አስታውሰዋል።
በዚህም፣ “በፍትህ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር፣ ሕግን የተላለፈ ፕሮግራም ስላቀረቡ፣ የፌደራል ፖሊስ ለዛሬ መጥሪያ አድርሶት ችሎት እንዲያቀርበው ቢታዘዝም፣ ‘የስዩም ተሾመ አድራሻው ስላልተገለጸልኝ ላቀርበው አልቻልኩም’ ብሎ ምላሽ ሰጥቷል ” ብለዋል።
አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በዚሁ ጉዳይ ዛሬ ምን አሉ ?
“ ከአሁን ቀደምም በስም ማጥፋት ወንጀል ፍርድ ቤት ከስሸው ተቀቷል። ፖሊስ ቋሚ አድራሻ ቢኖረውም በተደጋጋሚ ሄዶ እያየ ሰላምታ እየሰጠው ነው የሚመለሰው። ትምህርት ሳያገኝ በመቅረቱ ነው አሁንም ተመሳሳይ ድርጊት የፈጸመው።
መንግስት ቤት የሰጣቸው፣ ደሞዝ የሚከፍላቸው እና መኪና የተሰጣቸው የመንግስት አክቲቪስት ናቸው። አማራ ሲሆን የትም ይገኛል። ደብል ስታንዳርድ ነው። የፌደራል ፖሊስ የሰጠው መልስ ለእኛ አሳማኝ አይደለም ” ብለዋል።
አቶ ክርስቲያን ታደለ በዚሁ ጉዳይ ምን አሉ ?
“ ይሄ ‘ወስፌ ሲለግም ቂቤ አይወጋም’ የሚለው አባባል እውነት መሆኑን ያሳየ ነው። አቶ ስዩም ማለት የኢትዮጵያ መንግስት ጠባቂ ፖሊስ የመደበለት የመንግስት ተከፋይ ሃሜተኛ ነው።
እኔን አጅባችሁ ውሰዱኝና ቤቱን ላሳያችሁ። የመንግስት ሹመኛን የሚጠብቀው የፌደራል ፖሊስ አካል ነው።
እኛን የህዝብ እንደራሴዎችን ከቤተሰባችን ፊት ደብድቦና አዋርዶ ለማምጣት ያልተቸገረው ፌዴራል ፖሊስ፣ ላገኛቸው አልቻልኩም ማለቱ ስላቅ ነው። እውነቱን ንገረኝ ካላችሁኝ አቶ ስዩም ያልታሰረው አማራ ነኝ ስላላለ ነው ” ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል ተብሏል።
በመጨረሻም፣ “ የተከሳሾች ጠበቆች በደንበኞቻቸው ላይ የተላለፈው ፕሮግራም ሕግን የተላለፈ በመሆኑ ፖሊስ ያለምንም ምክንያት አቶ ስዩምን እንዲያቀርብ ይደረግልን ” ማለታቸውን የቅርብ ሰዎቻቸው ተናግረዋል።
“ ፍርድ ቤቱም በድጋሚ የፌደራል ፖሊስ ስዩም ተሾመን እንዲያቀርባቸው ለሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል ” ብለዋል።
N.B፦ ፌደራል ፓሊስ ፍርድ ቤት እንዲያቀርባቸው ተብለው ነበር የተባሉት አቶ ስዩም ተሾመ፣ ከሳምንት በፊት ባሳራጩት ዩቱዩብ ቻነል ስለነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው ሲናገሩ፣ “ቧያሌው ተንኮለኛ ነው። ከኔ በላይ ማን ምስክር አለ ያረገውን፤ እሰይ ቧያሌው ታሰረ ብዬ ስላልፎከርኩ ነው? መከራዬን አይደል ያበላኝ እሱ ምን ብዬ ስላልኩት ፋኖ ትጥቅ ይፍታ ' አይፈታም' ሲል የአማራን ህዝብ ታስበላላችሁ ሆን ብላችሁ ይሄ ሴራ ነው ስላልኳቸው ነው ይሄ ችግር የተፈጠረው ፤ የተለየ ወንጀል ሰርቼ አይደለም ፤ ገዱም እሱም ጠምደው መከራዬን ሲያበሉኝ የነበረው ፋኖ ትጥቅ አይፈታም ሲሉ ይሄ የድንቁርና ሃሳብ የአማራን ህዝብ ከፌዴራል መንግሥት ጋር ያጋጫል ፣ የማይሆን ቅርቃር ውስጥ ያስገባዋል፣ የአማራን ህዝብ ታስበላላችሁ፣ ወጣቱን ታስፈጃላችሁ እንዳልኩ ወጣት አስፈጅተዋል። እነዚህ ሰዎች ከዛ አልፈው ታጥቀው ' መንግሥት እንግለብጣልን ' ሲሉ መንግሥት ገልብጦ እስር ቤት ከቷቸዋል ስራቸው ያውጣቸው ” ሲሉ ተደምጠዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
⚫️ “ እኔን አጅባችሁ ውሰዱኝና ቤቱን ላሳያችሁ ” - አቶ ክርስቲያን ታደለ
🔴 “ ከአሁን ቀደምም በስም ማጥፋት ወንጀል ፍርድ ቤት ከስሸው ተቀቷል። ፖሊስ ቋሚ አድራሻ ቢኖረውም በተደጋጋሚ ሄዶ እያየ ሰላምታ እየሰጠው ነው የሚመለሰው ” - አቶ ዮሐንስ ቧያለው
የእነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌውን ጉዳይ የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የመንግስት አክቲቪስት” ሲሉ የጠሯቸውና “እነ ክርስቲያን ወንጀለኛ ናቸው” ያሉትን ግለሰብ ፌደራል ፓሊስ ማግኘት እንዳልቻለ ለፍርድ ቤት መግለጹን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
በዚህም፣ አቶ ስዩም ተሾመ የተባሉት ግለሰብ በቻናላቸው እነ አቶ ዮሐንስን ወንጀለኞች እንደሆኑ በመናገራቸው፣ እነ አቶ ዮሐንስም ክሰዋቸው ስለነበር ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ታዞ የነበረ ቢሆንም፣ ፌደራል ፓሊስ አቶ ስዩም ተሾመን ማግኘት አለመቻሉን ለፍርድ ቤት መግለጹን ነው ያስረዱት።
የእነ አቶ ዮሐንስ እና አቶ ክርስቲያን የቅርብ ሰዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ አቶ ዮሃንስ ቧያሌው እና ክርስቲያን ታደለ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ተከሰው ጉዳያቸው በመታዬት እያለ አቶ ስዩም ተሾመ መጋቢት 11/2017 ዓ/ም ባስተላለፉት ፕሮግራም ከተከሰሱበት ጉዳይ ጋር በተያያዘ ‘የአማራን ወጣት አስፈጅተዋል፣ ድሽቃ መሣሪያ መግዣ ጠይቀዋል’ ብለው እንደነበር አስታውሰዋል።
በዚህም፣ “በፍትህ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚያሳድር፣ ሕግን የተላለፈ ፕሮግራም ስላቀረቡ፣ የፌደራል ፖሊስ ለዛሬ መጥሪያ አድርሶት ችሎት እንዲያቀርበው ቢታዘዝም፣ ‘የስዩም ተሾመ አድራሻው ስላልተገለጸልኝ ላቀርበው አልቻልኩም’ ብሎ ምላሽ ሰጥቷል ” ብለዋል።
አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በዚሁ ጉዳይ ዛሬ ምን አሉ ?
“ ከአሁን ቀደምም በስም ማጥፋት ወንጀል ፍርድ ቤት ከስሸው ተቀቷል። ፖሊስ ቋሚ አድራሻ ቢኖረውም በተደጋጋሚ ሄዶ እያየ ሰላምታ እየሰጠው ነው የሚመለሰው። ትምህርት ሳያገኝ በመቅረቱ ነው አሁንም ተመሳሳይ ድርጊት የፈጸመው።
መንግስት ቤት የሰጣቸው፣ ደሞዝ የሚከፍላቸው እና መኪና የተሰጣቸው የመንግስት አክቲቪስት ናቸው። አማራ ሲሆን የትም ይገኛል። ደብል ስታንዳርድ ነው። የፌደራል ፖሊስ የሰጠው መልስ ለእኛ አሳማኝ አይደለም ” ብለዋል።
አቶ ክርስቲያን ታደለ በዚሁ ጉዳይ ምን አሉ ?
“ ይሄ ‘ወስፌ ሲለግም ቂቤ አይወጋም’ የሚለው አባባል እውነት መሆኑን ያሳየ ነው። አቶ ስዩም ማለት የኢትዮጵያ መንግስት ጠባቂ ፖሊስ የመደበለት የመንግስት ተከፋይ ሃሜተኛ ነው።
እኔን አጅባችሁ ውሰዱኝና ቤቱን ላሳያችሁ። የመንግስት ሹመኛን የሚጠብቀው የፌደራል ፖሊስ አካል ነው።
እኛን የህዝብ እንደራሴዎችን ከቤተሰባችን ፊት ደብድቦና አዋርዶ ለማምጣት ያልተቸገረው ፌዴራል ፖሊስ፣ ላገኛቸው አልቻልኩም ማለቱ ስላቅ ነው። እውነቱን ንገረኝ ካላችሁኝ አቶ ስዩም ያልታሰረው አማራ ነኝ ስላላለ ነው ” ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል ተብሏል።
በመጨረሻም፣ “ የተከሳሾች ጠበቆች በደንበኞቻቸው ላይ የተላለፈው ፕሮግራም ሕግን የተላለፈ በመሆኑ ፖሊስ ያለምንም ምክንያት አቶ ስዩምን እንዲያቀርብ ይደረግልን ” ማለታቸውን የቅርብ ሰዎቻቸው ተናግረዋል።
“ ፍርድ ቤቱም በድጋሚ የፌደራል ፖሊስ ስዩም ተሾመን እንዲያቀርባቸው ለሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል ” ብለዋል።
N.B፦ ፌደራል ፓሊስ ፍርድ ቤት እንዲያቀርባቸው ተብለው ነበር የተባሉት አቶ ስዩም ተሾመ፣ ከሳምንት በፊት ባሳራጩት ዩቱዩብ ቻነል ስለነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው ሲናገሩ፣ “ቧያሌው ተንኮለኛ ነው። ከኔ በላይ ማን ምስክር አለ ያረገውን፤ እሰይ ቧያሌው ታሰረ ብዬ ስላልፎከርኩ ነው? መከራዬን አይደል ያበላኝ እሱ ምን ብዬ ስላልኩት ፋኖ ትጥቅ ይፍታ ' አይፈታም' ሲል የአማራን ህዝብ ታስበላላችሁ ሆን ብላችሁ ይሄ ሴራ ነው ስላልኳቸው ነው ይሄ ችግር የተፈጠረው ፤ የተለየ ወንጀል ሰርቼ አይደለም ፤ ገዱም እሱም ጠምደው መከራዬን ሲያበሉኝ የነበረው ፋኖ ትጥቅ አይፈታም ሲሉ ይሄ የድንቁርና ሃሳብ የአማራን ህዝብ ከፌዴራል መንግሥት ጋር ያጋጫል ፣ የማይሆን ቅርቃር ውስጥ ያስገባዋል፣ የአማራን ህዝብ ታስበላላችሁ፣ ወጣቱን ታስፈጃላችሁ እንዳልኩ ወጣት አስፈጅተዋል። እነዚህ ሰዎች ከዛ አልፈው ታጥቀው ' መንግሥት እንግለብጣልን ' ሲሉ መንግሥት ገልብጦ እስር ቤት ከቷቸዋል ስራቸው ያውጣቸው ” ሲሉ ተደምጠዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤419😡136😭76🙏43🕊33😢32👏22🤔19😱8🥰4