#ሩስያ
ሩስያ ላልተወሰነ ጊዜ ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ወደ ውጭ መላክ አቆመች ፤ ይህ ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ይኖራል ተብሎ ተሰግቷል።
ሩስያ ፤ " የሀገር ውስጥ ገበያን ለማረጋጋት እንዲሁም የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎትን ለማሻሻል " በሚል ከአራት የቀድሞ የሶቪየት ሕብረት አባላት ውጭ ወደ #ሁሉም_ሀገራት የነዳጅ ምርቶችን ቤንዚን እና ናፍጣ መላክን ለጊዜው አግዳለች።
እገዳው ፦
- ቤላሩስ ፣
- ካዛኪስታን ፣
- አርሜኒያ እና ኪርጊስታን #አይመለከትም ተብሏል።
እገዳው " ጊዜያዊ ነው " የተባለ ሲሆን እስከመቼ እንደሚቆይ ሩስያ ያለችው ነገር የለም።
ሩሲያ ወደ ውጭ የምትልከው የናፍጣ ነዳጅ በቀን ወደ 900,000 በርሜል እንደሚገመት እና ሀገሪቱ በየቀኑ ከ60,000 እስከ 100,000 በርሜል ቤንዚን ወደ ውጭ እንደምትልክ የመንግስት የዜና ወኪሉ " ታስ " ዘግቧል።
የሩስያ የነዳጅ እገዳን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ሊያሳድር እንደሚችል እየተነገረ ይገኛል።
@tikvahethiopia
ሩስያ ላልተወሰነ ጊዜ ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ወደ ውጭ መላክ አቆመች ፤ ይህ ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ይኖራል ተብሎ ተሰግቷል።
ሩስያ ፤ " የሀገር ውስጥ ገበያን ለማረጋጋት እንዲሁም የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎትን ለማሻሻል " በሚል ከአራት የቀድሞ የሶቪየት ሕብረት አባላት ውጭ ወደ #ሁሉም_ሀገራት የነዳጅ ምርቶችን ቤንዚን እና ናፍጣ መላክን ለጊዜው አግዳለች።
እገዳው ፦
- ቤላሩስ ፣
- ካዛኪስታን ፣
- አርሜኒያ እና ኪርጊስታን #አይመለከትም ተብሏል።
እገዳው " ጊዜያዊ ነው " የተባለ ሲሆን እስከመቼ እንደሚቆይ ሩስያ ያለችው ነገር የለም።
ሩሲያ ወደ ውጭ የምትልከው የናፍጣ ነዳጅ በቀን ወደ 900,000 በርሜል እንደሚገመት እና ሀገሪቱ በየቀኑ ከ60,000 እስከ 100,000 በርሜል ቤንዚን ወደ ውጭ እንደምትልክ የመንግስት የዜና ወኪሉ " ታስ " ዘግቧል።
የሩስያ የነዳጅ እገዳን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ሊያሳድር እንደሚችል እየተነገረ ይገኛል።
@tikvahethiopia
❤1.12K👍1.01K😱229😢153👎92🕊40🙏15🥰13👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
" ስለ ትውልዱ ግድ ይለናል የምትሉ ኃላፊዎች መፍትሄ ስጡን " - ተማሪዎቹ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፤ " መፍትሄ የሚሰጠን አጥተን ያለ ትምህርት ቤታችን ቁጭ ብለናል ፤ ጊዜያችንም እየተቃጠለ ነው " ሲሉ አማረዋል። የባህር ዳር ዩንቨርሲቲ የ2016 ዓ/ም የ1ኛ ዓመት እና የሬሚድያል ተማሪዎች ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጎላቸው በኃላም መራዘሙ ይታወሳል። ነገር ግን እስካሁን ምንም አይነት ጥሪ…
#BahirDarUniversity
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች ጥሪ አደረገ።
በዚህም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደቡ Freshman ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስትከታትለው ቆይተው የማለፊያ ውጤት በማምጣት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደበ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ከመጋቢት 26 እስከ 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።
የምዝገባ ቦታውም ፦
➤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሰላም ግቢ
➤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ አባይ ግቢ ነው ተብሏል።
በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን አቋርጠው ለአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የሚያበቃ ውጤት ያላቸውና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞሉ ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ያወጣው ጥሪ በማካካሻ መርሐ ግብር (Remedial Program) በ2016 ዓ/ም አዲስ የተመደቤ ተማሪዎችን #አይመለከትም ተብሏል።
Via @tikvahuniversity
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች ጥሪ አደረገ።
በዚህም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደቡ Freshman ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስትከታትለው ቆይተው የማለፊያ ውጤት በማምጣት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደበ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ከመጋቢት 26 እስከ 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።
የምዝገባ ቦታውም ፦
➤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሰላም ግቢ
➤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ አባይ ግቢ ነው ተብሏል።
በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን አቋርጠው ለአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የሚያበቃ ውጤት ያላቸውና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞሉ ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ያወጣው ጥሪ በማካካሻ መርሐ ግብር (Remedial Program) በ2016 ዓ/ም አዲስ የተመደቤ ተማሪዎችን #አይመለከትም ተብሏል።
Via @tikvahuniversity
❤174😡77🕊33🙏21😭17🥰8😢7🤔6😱6👏2