TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AxumUniversity

በጦርነት ምክንያት አክሱም ዩኒቨርሲቲ አቁሟቸው ነበሩትን አገልግሎቶች ማስጀመሩን ለማወቅ ተቸሏል።

ዩኒቨርሲቲው ለቀድሞ ተማሪዎቹ ፦
➭ ኦፊሽያል ትራንስክሪፕት
➭ ስቱደንት ኮፒ
➭ ጊዚያዊ ሰርተፊኬት
➭ የዲግሪ ማረጋገጫ
➭ እንግሊዝኛ የማስተማሪያ ቋንቋነት ማረጋገጫ መስጠት መጀመሩን ገልጿል።

በመሆኑም የቀድሞ ተመራቂዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በዩኒቨርሲቲው በአካል በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በሁለት ወይም በሦስት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ኦሪጅናል ዲግሪ መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ዓመታት በትግራይ ጦርነት ምክንያት የተቋረጠውን የመማር ማስተማር ስራ ለማስጀመርና ተማሪዎቹን ለመቀበል ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ለማወቅ ችለናል።

More : @tikvahuniversity
👍1.51K165👎93🕊74🙏47🥰27😱25😢6