TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ቦረና

" በቡድንም ሆነ በተናጠል ድጋፍ መሰብሰብ አይቻልም " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

በቦረና ዞን በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለማድረግ በቡድንም ሆነ በተናጠል መሰብሰብ እንደማይፈቀድ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አሳሰበ።

የክልሉ መንግስት ፤ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች በተለይ በቦረና ዞን በተከታታይ አምስት የዝናብ ወቅት ዝናብ አለመጣሉን ተከትሎ ድርቅ መከሰቱ አስታውሷል።

በተከሰተዉ ድርቅ ምክንያትም መንግስት ባቀረበዉ ጥሪ መሠረት ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች በተለያዩ መንገዶች በገንዘብና በዓይነት ድጋፍ እየተሰበሰበ ይገኛል ብሏል።

ከዚህ በኋላ ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ወይም ከኦሮሚያ ቡሳ ጎኖፋ እዉቅና ዉጭ #በቡድንም ሆነ #በተናጠል ድጋፍ ማድረግ የማይፈቀድ መሆኑን አሳስቧል።

ይህም የሚሰበሰበዉን ድጋፍ በአግባቡ ለማስተዳደር፣ ፍትሓዊ በሆነና ግልፅነት ባለዉ መንገድ ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ውሳኔ መሆኑን የክልሉ መንግሥት ገልጿል።

#ኦቢኤን

@tikvahethiopia
👎5.77K👍651🤔188😢82😱48🕊1715🥰13🙏9
#ቦረና

በ ' ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ' የተሰራ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።

ፋውንዴሽኑ በቦረና ዞን ሚዮ ወረዳ፣ በቦኩ ሉቦማ መንደር እና ዱቡሉቅ ወረዳ የንፁህ ውሃ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ አስመርቋል።

ፕሮጀክቱ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ እንደወጣበት ተመላክቷል።

በዝግጅቱ ላይ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ የአካባቢው ማህበረሰብ እና የመንግስት ተወካዮች ተገኝተዋል።

የውሃ ፕሮጀክቱ የሁለቱን ወረዳዎች 52,325 ነዋሪዎችን የመጠጥ ውሃ ችግር ያቃልላል ተብሎ ይጠበቃል።

ፎቶ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን

@tikvahethiopia
914👍466👎161🙏56😢26🕊17😱3