TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ቦረና
🗣 የቦረና ዞን ተልተሌ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጉዮ ቱሩ ፦
" ቆሪ ጉዮ የተባለው ልጄ 16 ዓመቱ ነበር። ጤናማ እና ጠንካራ ነበር። ነገር ግን በረሃብ ምክንያት ታመመ። ምንም አልነበረንም። የነበሩን ከብቶች በድርቁ አልቀዋል።
ሆስፒታል ወስደነው ነበር። ችግሩ ከምግብ እጥረት ጋር የተያያዘ ነው አሉን። ከዚያ ከሆስፒታል እንደተመለሰ ሞተ። "
🗣 የቦረና ዞን የተልተሌ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ኤንጌ ዋሪዮ፦
" በወረዳው ከተከሰተ የምግብ እጥረት ጋር ተያይዞ የሰባት ሰዎች ሕይወት አልፏል።
ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን ካጡት መካከል የሁለት ወር ጨቅላ ይገኝበታል።
በተልተሌ ወረዳ፣ ከሁለት ወር ህጻን ጀምሮ እስከ አዛውንቶች ድረስ በረሃብ ምክንያት ሰባት የሚሆኑ ሰዎች ሞተዋል።
ሰዎች ያለ ምግብ ብዙ ቀን እየቆዩ ነው። ያሏቸውም ከብቶች አልቀውባቸዋል። "
🗣 የተልተሌ ወረዳ የአደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኃላፊ ገልመ ሞሉ፦
" በረሃብ ምክንያት ሰዎች እየሞቱ ነው ለሚለው ስለሚለው የደረሰኝ መረጃ የለም።
ይሁን እንጂ ሕጻናት አረጋውያን በምግብ እጥረት ምክንያት ከቀላል በሽታዎች ማገገም እየቻሉ አይደለም። "
CREDIT : #BBC
@tikvahethiopia
🗣 የቦረና ዞን ተልተሌ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጉዮ ቱሩ ፦
" ቆሪ ጉዮ የተባለው ልጄ 16 ዓመቱ ነበር። ጤናማ እና ጠንካራ ነበር። ነገር ግን በረሃብ ምክንያት ታመመ። ምንም አልነበረንም። የነበሩን ከብቶች በድርቁ አልቀዋል።
ሆስፒታል ወስደነው ነበር። ችግሩ ከምግብ እጥረት ጋር የተያያዘ ነው አሉን። ከዚያ ከሆስፒታል እንደተመለሰ ሞተ። "
🗣 የቦረና ዞን የተልተሌ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ኤንጌ ዋሪዮ፦
" በወረዳው ከተከሰተ የምግብ እጥረት ጋር ተያይዞ የሰባት ሰዎች ሕይወት አልፏል።
ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን ካጡት መካከል የሁለት ወር ጨቅላ ይገኝበታል።
በተልተሌ ወረዳ፣ ከሁለት ወር ህጻን ጀምሮ እስከ አዛውንቶች ድረስ በረሃብ ምክንያት ሰባት የሚሆኑ ሰዎች ሞተዋል።
ሰዎች ያለ ምግብ ብዙ ቀን እየቆዩ ነው። ያሏቸውም ከብቶች አልቀውባቸዋል። "
🗣 የተልተሌ ወረዳ የአደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኃላፊ ገልመ ሞሉ፦
" በረሃብ ምክንያት ሰዎች እየሞቱ ነው ለሚለው ስለሚለው የደረሰኝ መረጃ የለም።
ይሁን እንጂ ሕጻናት አረጋውያን በምግብ እጥረት ምክንያት ከቀላል በሽታዎች ማገገም እየቻሉ አይደለም። "
CREDIT : #BBC
@tikvahethiopia
😢940👍373🙏32👎21😱13🥰4🤔4❤2🕊2
#ቦረና
" በቡድንም ሆነ በተናጠል ድጋፍ መሰብሰብ አይቻልም " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት
በቦረና ዞን በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለማድረግ በቡድንም ሆነ በተናጠል መሰብሰብ እንደማይፈቀድ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አሳሰበ።
የክልሉ መንግስት ፤ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች በተለይ በቦረና ዞን በተከታታይ አምስት የዝናብ ወቅት ዝናብ አለመጣሉን ተከትሎ ድርቅ መከሰቱ አስታውሷል።
በተከሰተዉ ድርቅ ምክንያትም መንግስት ባቀረበዉ ጥሪ መሠረት ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች በተለያዩ መንገዶች በገንዘብና በዓይነት ድጋፍ እየተሰበሰበ ይገኛል ብሏል።
ከዚህ በኋላ ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ወይም ከኦሮሚያ ቡሳ ጎኖፋ እዉቅና ዉጭ #በቡድንም ሆነ #በተናጠል ድጋፍ ማድረግ የማይፈቀድ መሆኑን አሳስቧል።
ይህም የሚሰበሰበዉን ድጋፍ በአግባቡ ለማስተዳደር፣ ፍትሓዊ በሆነና ግልፅነት ባለዉ መንገድ ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ውሳኔ መሆኑን የክልሉ መንግሥት ገልጿል።
#ኦቢኤን
@tikvahethiopia
" በቡድንም ሆነ በተናጠል ድጋፍ መሰብሰብ አይቻልም " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት
በቦረና ዞን በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለማድረግ በቡድንም ሆነ በተናጠል መሰብሰብ እንደማይፈቀድ የኦሮሚያ ክልል መንግስት አሳሰበ።
የክልሉ መንግስት ፤ በክልሉ አንዳንድ ዞኖች በተለይ በቦረና ዞን በተከታታይ አምስት የዝናብ ወቅት ዝናብ አለመጣሉን ተከትሎ ድርቅ መከሰቱ አስታውሷል።
በተከሰተዉ ድርቅ ምክንያትም መንግስት ባቀረበዉ ጥሪ መሠረት ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች በተለያዩ መንገዶች በገንዘብና በዓይነት ድጋፍ እየተሰበሰበ ይገኛል ብሏል።
ከዚህ በኋላ ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ወይም ከኦሮሚያ ቡሳ ጎኖፋ እዉቅና ዉጭ #በቡድንም ሆነ #በተናጠል ድጋፍ ማድረግ የማይፈቀድ መሆኑን አሳስቧል።
ይህም የሚሰበሰበዉን ድጋፍ በአግባቡ ለማስተዳደር፣ ፍትሓዊ በሆነና ግልፅነት ባለዉ መንገድ ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ውሳኔ መሆኑን የክልሉ መንግሥት ገልጿል።
#ኦቢኤን
@tikvahethiopia
👎5.77K👍651🤔188😢82😱48🕊17❤15🥰13🙏9
#ቦረና
በ ' ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ' የተሰራ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።
ፋውንዴሽኑ በቦረና ዞን ሚዮ ወረዳ፣ በቦኩ ሉቦማ መንደር እና ዱቡሉቅ ወረዳ የንፁህ ውሃ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ አስመርቋል።
ፕሮጀክቱ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ እንደወጣበት ተመላክቷል።
በዝግጅቱ ላይ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ የአካባቢው ማህበረሰብ እና የመንግስት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የውሃ ፕሮጀክቱ የሁለቱን ወረዳዎች 52,325 ነዋሪዎችን የመጠጥ ውሃ ችግር ያቃልላል ተብሎ ይጠበቃል።
ፎቶ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን
@tikvahethiopia
በ ' ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ' የተሰራ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።
ፋውንዴሽኑ በቦረና ዞን ሚዮ ወረዳ፣ በቦኩ ሉቦማ መንደር እና ዱቡሉቅ ወረዳ የንፁህ ውሃ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ አስመርቋል።
ፕሮጀክቱ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ እንደወጣበት ተመላክቷል።
በዝግጅቱ ላይ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ የአካባቢው ማህበረሰብ እና የመንግስት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የውሃ ፕሮጀክቱ የሁለቱን ወረዳዎች 52,325 ነዋሪዎችን የመጠጥ ውሃ ችግር ያቃልላል ተብሎ ይጠበቃል።
ፎቶ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን
@tikvahethiopia
❤914👍466👎161🙏56😢26🕊17😱3