#STEMpower #VISA #TikvahEthiopia
ስቴም ፓወር፣ ቪዛና ቲክቫህ ኢትዮጵያ በመተባበር ሲያዘጋጁት የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
ስቴም ፓወር (STEMpower) ፣ ቪዛ (Visa) እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ (TIKVAH-ETH) በጋራ በመሆን ሲያዘጋጁት የቆዩትና በአስር ዙር የተሰጠው የስራ ፈጠራ እና መሰረታዊ የፋይናንስ ክህሎት ስልጠና ተገባዷል።
ላለፉት ሦስት ዓመታት በአስር ዙር ሲሰጥ በነበረው በዚህ ሥልጠና በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል 16,400 ሰልጣኞች ስልጠናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል። ይህም በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት ያሳየ ነበር።
በዚህ ሥልጠና፥ 2,420 በሰልጣኞች ያሰለጠኑ ሲሆን ሥልጠናውን በአግባቡ ተከታትለው ከጨረሱ ሰልጣኞች ውስጥ ከ50 በላይ የሚሆኑት ጀማሪ ቢዝነሶችን በራሳቸው ጀምረው ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል።
በዚህ ፕሮጀክት ከሥልጠናው ባሻገር ነፃ የቢዝነስ ማማከር እና ለፕሮቶ ታይፕ መስሪያ የሚሆን የማሽነሪ እና ጥሬ እቃ ለሰልጣኞች ሲያቀርብ ቆይቷል።
በዚህ አጋጣሚ ወጣቶችን በስፋት ተጠቃሚ ባደረገውና ለውጥ መፍጠር በቻለው በዚህ ፕሮጀክት ላይ የተሳተፉ አጋር አካላትን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሊያመሰግን ይወዳል።
@tikvahethiopia
ስቴም ፓወር፣ ቪዛና ቲክቫህ ኢትዮጵያ በመተባበር ሲያዘጋጁት የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
ስቴም ፓወር (STEMpower) ፣ ቪዛ (Visa) እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ (TIKVAH-ETH) በጋራ በመሆን ሲያዘጋጁት የቆዩትና በአስር ዙር የተሰጠው የስራ ፈጠራ እና መሰረታዊ የፋይናንስ ክህሎት ስልጠና ተገባዷል።
ላለፉት ሦስት ዓመታት በአስር ዙር ሲሰጥ በነበረው በዚህ ሥልጠና በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል 16,400 ሰልጣኞች ስልጠናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል። ይህም በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት ያሳየ ነበር።
በዚህ ሥልጠና፥ 2,420 በሰልጣኞች ያሰለጠኑ ሲሆን ሥልጠናውን በአግባቡ ተከታትለው ከጨረሱ ሰልጣኞች ውስጥ ከ50 በላይ የሚሆኑት ጀማሪ ቢዝነሶችን በራሳቸው ጀምረው ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል።
በዚህ ፕሮጀክት ከሥልጠናው ባሻገር ነፃ የቢዝነስ ማማከር እና ለፕሮቶ ታይፕ መስሪያ የሚሆን የማሽነሪ እና ጥሬ እቃ ለሰልጣኞች ሲያቀርብ ቆይቷል።
በዚህ አጋጣሚ ወጣቶችን በስፋት ተጠቃሚ ባደረገውና ለውጥ መፍጠር በቻለው በዚህ ፕሮጀክት ላይ የተሳተፉ አጋር አካላትን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሊያመሰግን ይወዳል።
@tikvahethiopia
👍354❤59👎11👏9🥰5🕊5😱2🙏1