TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጋብቻ

እየተጠናቀቀ ባለው በ2015 ዓ/ም የጋብቻ ፍቺ የፈፀሙ እና የተመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ባለትዳሮች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር #በእጥፍ እንደበለጠ ታውቋል።

የአ/አ ሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በሰጡት ቃል፤ " በ2015 ዓ/ም በጀት አመት 4,696 ሰዎች ፍቺ አስመዝግበዋል ፤ አምና መጥተው ያስመዘገቡት 2,937 ሰዎች ነበሩ " ብለዋል።

ምዝገባው ነው የጨመረው እንጂ ፍቺው ከዚህም በላይ ሊሆን ይችላል ሲሉ ዳይሬክተሩ አክለዋል።

የፍቺ ሁኔታ ከእጥፍ በላይ ጭማሪ ቢያሳይም ሂደቱ ፍርድ ቤትን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የሚከናወን በመሆኑ ትክክለኛውን ቁጥር ለማውቅ አዳጋች እንደሆነ አቶ ዮሴፍ ገልጸዋል።

" ፍ/ቤት ላይ የሚፈፀመውን ፍቺ እዛው ወቅታዊ ምዝገባውን የማከናወን ስራ በዚህ አመት አቅደን አልተሳካም ሚቀጥለው አመት እየተነጋገርን ነው ፍርድ ቤት ሆነን ምዝገባ የሚከናወንበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለን እንጠብቃለን። " ብለዋል።

" በዚህ መንገድ ትክክለኛውን ዳታ ፍቺ እየጨመረ ነው ወይስ እየቀነሰ ነው የሚለውን ውሳኔ ለመስጠት እንችላለን " ያሉት አቶ ዮሴፍ " አሁን ላይ ግን የኛ ምዝገባ ሰው ፍልጎ ፍቺውን በተለያየ አግባብ ለንብረት ክፍፍል ፣ ከመታወቂያ ዲጂታላይዝ መደረግ ጋር ተያይዞ የጋብቻ ሁኔታ ፍቺ የማስባል እና ሌሎች ነገሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ... በዛ ምክንያት እኛ ጋር ምዝገባው ከአምና ከፍ ብሏል የሚል ድምዳሜ ነው የያዝነው " ሲሉ ተናግረዋል።

#ቪኦኤ

@tikvahethiopia
👍544😢21282👎44😱42🕊13👏12🥰8🙏7