TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የት ገቡ ?

(በባይሽ ኮልፌ)

#እስካሁን_አልተገኙም !

👉 ወጣት አብርሀም በየነ ከ3 ዓመት በፊት ከሚኖርበት ሀዋሳ ወደ ወልቂጤ ሚቄ የሚባል ቦታ መጥቶ ወረዳ ውስጥ ስራውን እየሰራ መስከረም 25 " እናቴ ናፍቃኛለች አይቻት ልምጣ " ብሎ ለጓደኞቹ ነግሮ ከቢሮና ከተከራየበት ቤት ቢወጣም እናቱ ጋር ሳይደርስ ወደ ቤቱም ሳይመለስ የት እንደገባ ጠፍቶ 2 ወር አልፎታል። በየቀኑ ይደውልላት የነበረው እናት " የምሄድበት ግራ ገባኝ ምን ልሁን? " እያለች ቤተክርስቲያን እየዞረች በፀሎት እያነባች ነው 😭 ስልኳ-0985132283 (እልፍነሽ-እናት)

👉 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግራውንድ ቴክንሽያን ዳዊት ምትኩ ከሚኖርበት አምባሳደር ኮንዶሚኒየም አካባቢ ድንገት እንደወጣ ሳይመለስ 24 ቀናት ተቆጥረዋል። እናትና አባት እንዲሁም እህቱ እያለቀሱ መንገድ ለመንገድ እየተንከራተቱ ነው። (0941213747-የእህቱ ስልክ)

👉 የ2 ህፃናት አባት በሙያው ጎበዝ ሼፍ የሆነው ዘሪሁን ቢሰጥ ሀያት አካባቢ የሚከፈት አዲስ ሆቴል ውስጥ ስራ ሊጀምር እንደሆነ ለባለቤቱ ነግሯት ሰኞ ህዳር 12 ዓ/ም በስራው ዙሪያ ለመነጋገር ቀጠሮ እንዳለውና በዛውም ኬጂ የምትማረው የመጀመሪያ ልጁን ኮተቤ የሚገኘው አፕል አካዳሚ ላድርሳት ብሎ እንደወጣ ሳይመለስ ቀርቷል። 18 ቀናት ተቆጥረዋል ፤ ባለቤቱ "መቋቋም አቃተኝ፣ አመመኝ ድፍን ያለነገር ሆነብኝ " እያለች ነው። (0920181284-ሰብለ ባለቤቱ)

መልዕክቱን ሼር በማድረግ ያፋልጉን !

(ባየሽ ኮልፌ)

@tikvahethiopia
😢883👍573🙏64😱38🕊2412👎10
#Amhara

#እቅድ፦ 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ለመመዝገብ

#እስካሁን_የተመዘገቡት ፦ 2,937,556 ተማሪዎች

በአማራ ክልል ለዘንድሮ ዓመት ትምህርት ይመዘገባሉ ተብለው ከታሰቡት 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎች መመዝገብ የተቻለው 2,937,556 ተማሪዎችን እንደሆነ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ይህ ከቅድመ መደበኛ እስከ 2ኛ ደረጃ ሲሆን ካለፉት ዓመታት ሲነፃፀር እቅዱ አጥጋቢ እንዳልሆነ አመልክቷል።

የሚጠበቀውን ያህል ተማሪዎች እንዳይመዘገቡ ከሆነበት ምክንያቶች አንዱ በክልሉ ውስጥ በልዩ ልዩ ቦታዎች ያለው የትጥቅ ግጭት መሆኑ ተነግሯል።

አንዳንድ ዞኖች እስካሁን ጭራሽ ምዝገባም ያልጀመሩ ሲሆን እነዚህም የምዕራብ አማራ አካባቢዎች ፣ ምስራቅ ጎጃም ፣ ምዕራብ ጎጃም ደብረማርቆስ ፣ ሰሜን ጎጃም እንደሆኑ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

በክልሉ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ተፅእኖ አሳድሮብናል ያለው ትምህርት ቢሮ አንፃራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች ላይ የተማሪ ምዝገባ መከናወኑን አመልክቷል። አንዳንድ ዞኖችም የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግበዋል ሲል አክሏል።

አሁንም የምዝገባ ቀኑ ያልተገደበ ሲሆን ዞኖች ጎን ለጎን የመማር ማስተማር ስራውን እና ምዝገባውን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው ማለቱን ቪኦኤ ዘገቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
😢39152😡36🙏24😱17🕊17🥰10