TIKVAH-ETHIOPIA
#TikvahFamily በትላንትናው ዕለት የ2ኛው ዙር የመማሪያ መፅሀፍትና ቁሳቁስ የማሰባሰብ ዘመቻ መካሄድ ጀምሯል። በመጀመሪያው ዙር በጥቂት ቀናት 7 ሺህ በላይ መፅሀፍትና 3 ዴስክቶፕ ኮምፒዩተር መሰብሰቡና በአማራ ክልልና በደቡብ ክልል ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች፣ በአዲስ አበባ ላለ የህዝብ ቤተመፅሀፍ መከፋፈሉ ይታወሳል። በዚህኛው ዙር በመፅሀፍት ደረጃ ከ30 ሺህ በላይ ለመሰብሰብ ታስቧል። በዚህ ዙር…
#ምስጋና
በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ በኩል በየዓመቱ የመማሪያ መፅሀፍት ሲሰባሰብ 5 ዓመታትን ደፍኗል። (በኮቪድ ወረርሽኝ እና ጦርነት ምክንያት የተቋረጡትን አይጨምርም)
ባለፈው ክረምት ላይ በጀመረው 5ኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ (በአዲስ አበባ) መፅሀፍት ተሰብስበው ለት/ቤቶች ተሰጥቷል።
የዚሁ ቀጣይ የሆነ ሁለተኛ ዙር የማሰባሰብ ስራ ከቅዳሜ አንስቶ እየተካሄደ ነው።
ስራው ከመፅሀፍ ባለፈ የትምህርት መሳሪያዎችን ያካተተ ሲሆን ዘመቻው ከተጀመረ ወዲህ #ከየቤተሰቦቻችን መኖሪያ አካባቢ በመሄድ የተሰበሰቡ ፦
ትላንት ቅዳሜ ፦
- አቶ ዳንኤል ቦጋለ ከልጃቸው ነብዩ ዳንኤልና ከመላ ቤተሰባቸው ጋር መደበኛ መፅሀፍት 58 ፣ አጋዥ 2 ፣ የህፃናት 2 ፣ ልብወለደ 1 ፣ የግል ት/ቤት 11 መፅሀፍት አበርክተዋል።
- ወ/ሮ ኑሪያ አደም ከልጆቻቸው ሲያ አህመዝ ፣ ሀናን አህመድ፣ ረምላ አህመድ ከመላው ቤተሰባቸው ጋር 9 አጋዥ መፅሀፍት ፣ መዝገበ ቃላት 3 ፣ መደበኛ 19 መፅሀፍት እና አንድ ሞኒተር አበርክተዋል።
- ወ/ሮ ሰብለ ተሾመ ከልጆቻቸው በረከት ፍስሃ፣ በእምነት ፍስሃ፣ በፍቅር ፍስሃ ከመላው ቤተሰባቸው ጋር 38 መደበኛ መፅሀፍ 5 አጋዥ መፅሀፍ አበርክተዋል።
- አንድ የቤተሰባችን አባል ስሙን መግለፅ ያልፈለገ የ5 ሺህ ብር 106 መፅሀፍ ገዝቶ አስረክቧል።
- ዶ/ር አለማየሁ ሀብተገብርኤል ከልጆቻቸው ቤተልሄም ፣ መክሊት፣ ዳግማዊት እና በመላው ቤተሰባቸው ስም አንድ #ከለር_ፕሪንተር እና #ሞኒተር አበርክተዋል።
#ይቀጥላል
በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ በኩል በየዓመቱ የመማሪያ መፅሀፍት ሲሰባሰብ 5 ዓመታትን ደፍኗል። (በኮቪድ ወረርሽኝ እና ጦርነት ምክንያት የተቋረጡትን አይጨምርም)
ባለፈው ክረምት ላይ በጀመረው 5ኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ (በአዲስ አበባ) መፅሀፍት ተሰብስበው ለት/ቤቶች ተሰጥቷል።
የዚሁ ቀጣይ የሆነ ሁለተኛ ዙር የማሰባሰብ ስራ ከቅዳሜ አንስቶ እየተካሄደ ነው።
ስራው ከመፅሀፍ ባለፈ የትምህርት መሳሪያዎችን ያካተተ ሲሆን ዘመቻው ከተጀመረ ወዲህ #ከየቤተሰቦቻችን መኖሪያ አካባቢ በመሄድ የተሰበሰቡ ፦
ትላንት ቅዳሜ ፦
- አቶ ዳንኤል ቦጋለ ከልጃቸው ነብዩ ዳንኤልና ከመላ ቤተሰባቸው ጋር መደበኛ መፅሀፍት 58 ፣ አጋዥ 2 ፣ የህፃናት 2 ፣ ልብወለደ 1 ፣ የግል ት/ቤት 11 መፅሀፍት አበርክተዋል።
- ወ/ሮ ኑሪያ አደም ከልጆቻቸው ሲያ አህመዝ ፣ ሀናን አህመድ፣ ረምላ አህመድ ከመላው ቤተሰባቸው ጋር 9 አጋዥ መፅሀፍት ፣ መዝገበ ቃላት 3 ፣ መደበኛ 19 መፅሀፍት እና አንድ ሞኒተር አበርክተዋል።
- ወ/ሮ ሰብለ ተሾመ ከልጆቻቸው በረከት ፍስሃ፣ በእምነት ፍስሃ፣ በፍቅር ፍስሃ ከመላው ቤተሰባቸው ጋር 38 መደበኛ መፅሀፍ 5 አጋዥ መፅሀፍ አበርክተዋል።
- አንድ የቤተሰባችን አባል ስሙን መግለፅ ያልፈለገ የ5 ሺህ ብር 106 መፅሀፍ ገዝቶ አስረክቧል።
- ዶ/ር አለማየሁ ሀብተገብርኤል ከልጆቻቸው ቤተልሄም ፣ መክሊት፣ ዳግማዊት እና በመላው ቤተሰባቸው ስም አንድ #ከለር_ፕሪንተር እና #ሞኒተር አበርክተዋል።
#ይቀጥላል
👍443🙏31❤9🥰5😱5👎2🤔1😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
ዕግዱ ተነሳ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ጥሎት የነበረውን #ጊዜያዊ ዕግድ ዛሬ አርብ ማንሳቱን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#ምስጋና
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ፈጣን ምላሽ ምስጋና አቅርባለች።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማኅበረ
ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ፣ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. ያስተላለፈውን ጊዜያዊ እገዳ እንዲያነሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ያቀረበችውን ጥያቄ በመቀበል፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተጻፈለት ደብዳቤ እንደደረሰው ሳይውል ሳያድር ጊዜያዊ እገዳውን አንስቷል።
በዚህም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችውን ጥያቄ በአዎንታ ተመልክቶ አፋጣኝ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ፣ ከፍ ያለ ምስጋናን ማቅረቧን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አሳውቋል።
ፅ/ቤቱ ፤ " ለወደፊቱም ተቋማዊ ግንኙነታችንን የበለጠ በማጠናከር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መኾናችንን እንገልጻለን " ብሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ፈጣን ምላሽ ምስጋና አቅርባለች።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማኅበረ
ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ፣ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. ያስተላለፈውን ጊዜያዊ እገዳ እንዲያነሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ያቀረበችውን ጥያቄ በመቀበል፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተጻፈለት ደብዳቤ እንደደረሰው ሳይውል ሳያድር ጊዜያዊ እገዳውን አንስቷል።
በዚህም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችውን ጥያቄ በአዎንታ ተመልክቶ አፋጣኝ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ፣ ከፍ ያለ ምስጋናን ማቅረቧን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አሳውቋል።
ፅ/ቤቱ ፤ " ለወደፊቱም ተቋማዊ ግንኙነታችንን የበለጠ በማጠናከር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መኾናችንን እንገልጻለን " ብሏል።
@tikvahethiopia
👍830👎236❤75🕊17😢12😱5🙏2
በሀገራችን አንዳንድ መልካም የስራ ስነምግባር የጎደላቸው ፣ ከአሸከርካሪዎች ጉቦ ካልተቀበሉ ቀኑ መሽቶ የማይነጋ የሚመስላቸው ፣ አንዳንዴም ሆን ብለው ምክንያት ፈልገው የቅጣት ወረቀት ለመፃፍ በኃላም #ጉቦ ለመቀበል የማይፈነቅሉት ድንጋይ የሌላቸው ፣ ፀሀዩ በረታብኝ ፥ ዝናቡም አካፍብኝ ብለው የሚጠለሉ የትራፊክ የፖሊስ አባላት እንዳሉት ሁሉ ፦
- ለስራቸው ታማኝ
- ህግን አክባሪ
- ቅን አገልጋይ
- ፀሀይ ፣ ዝናብ ሳይሉ ህዝብን አክብረው የሚሰሩ በርካታ የትራፊክ ፖሊስ አባላት አሉ።
ለእነዚህ አይነት ህዝብን አክብረው ምንም አይነት ሁኔታ ሳይገድባቸው ለሚሰሩ የትራፊክ ፖሊስ አባላት #ምስጋና ይገባል።
በሀገራችን ካሉ ከተሞች አንዷ በሆነችው የሰላም ተምሳሌቷ #ድሬዳዋ ❤️ የትራፊክ ፖሊስ አባላቶቿ በተለያየ ጊዜ በመልካም ስነምግባራቸው ስማቸው ተደጋግሞ ይነሳል።
ትላንትና በከተማው ከባድ ዘናብ ዘንቦ በነበረበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ እንዳይከሰት አንድ የትራፊክ ፖሊስ አባል በዝናብ ውስጥ ሆኖ ስራውን ሲያከናውን የሚያሳይ የተቀረጹ ቪድዮዎች እና ፎቶዎች ብዙዎች በማህበራዊ ሚዲያ ሲያጋሩት ውለዋል።
@tikvahethiopia
- ለስራቸው ታማኝ
- ህግን አክባሪ
- ቅን አገልጋይ
- ፀሀይ ፣ ዝናብ ሳይሉ ህዝብን አክብረው የሚሰሩ በርካታ የትራፊክ ፖሊስ አባላት አሉ።
ለእነዚህ አይነት ህዝብን አክብረው ምንም አይነት ሁኔታ ሳይገድባቸው ለሚሰሩ የትራፊክ ፖሊስ አባላት #ምስጋና ይገባል።
በሀገራችን ካሉ ከተሞች አንዷ በሆነችው የሰላም ተምሳሌቷ #ድሬዳዋ ❤️ የትራፊክ ፖሊስ አባላቶቿ በተለያየ ጊዜ በመልካም ስነምግባራቸው ስማቸው ተደጋግሞ ይነሳል።
ትላንትና በከተማው ከባድ ዘናብ ዘንቦ በነበረበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ እንዳይከሰት አንድ የትራፊክ ፖሊስ አባል በዝናብ ውስጥ ሆኖ ስራውን ሲያከናውን የሚያሳይ የተቀረጹ ቪድዮዎች እና ፎቶዎች ብዙዎች በማህበራዊ ሚዲያ ሲያጋሩት ውለዋል።
@tikvahethiopia
❤5.42K🙏643👏342🕊70🥰57😡26😢25🤔19😱9😭6