TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Woldia በወልድያ ከተማ የሰዓት እላፊ ታወጀ  ፤ ጥብቅ የሆኑ ክልከላዎችም ተጥለዋል። ወልድያ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ኮማንድ ፖስት ላልተወሰነ ጊዜ የሚቆይ የሰዓት እላፊ ገደብ እና ክልከላ ማስቀመጡ ተገልጿል። ክልከላዎቹ ፦ - ጭፈራ ቤቶች፥ ካፍቴሪያዎች፣ ሬስቶራንቶች እና የመሳሰሉት ማንኛውም መጠጥ ቤቶች ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት መስጠት አይችሉም። - ለባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች…
#ኮምቦልቻ

ከዛሬ ጀምሮ ኮምቦልቻ ውስጥ ሰልፍ ማድረግ አድማ መጥራት ተከለከለ ፤ የሰዓት እላፊም ታውጇል።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከተወያየ በኋላ ክልከላዎች አውጥቷል።

ምን ክልከላዎች ተጣሉ ?

1ኛ. ከዛሬ ሚያዚያ 3/2015 ዓ.ም ጀምሮ ሰልፍ ማድረግ አድማ መጥራት ተከልክሏል።

2ኛ. ከተፈቀደላቸው የመንግስት የጸጥታ መዋቅሮች ውጭ ማንኛውም ሰው የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

3ኛ. ከተፈቀደላቸው የመንግስት ተሽከርካሪዎች እና አምቡላንሶች ውጭ ማንኛውም ባለ ሁለትና ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ ተከልክለዋል።

4ኛ. የመጠጥእና ምግብ ቤቶችም አገልግሎት መስጠት የሚችሉት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ብቻ ነው ተብሏል።

5ኛ. የሰዎች እንቅስቃሴን በተመለከተ የተርሃዊ ሶላት ከመኖሩ ጋር ተያይዞ እስከ ምሽቱ 3:00 ሰዓት ብቻ መንቀሳቀስ የተፈቀደ ሲሆን ከ3:00 ሰዓት ውጭ የማንኛውም ግለሰብ እንቅስቃሴ ተገድቧል።

6ኛ. በህግ ከተፈቀደላቸው የጸጥታ መዋቅሮች ውጭ የጸጥታ መዋቅሮችን ልብስ ለብሶ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

ክልከላዎቹ ከዛሬ ጀምሮ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

መረጃው የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት ነው።

@tikvahethiopia
👎1.55K👍78273🕊36🙏15😢7😱1