TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይፈለጋል #Wanted ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል። አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠርጠሪው እንደተያዘ በማስመሰል የሚያሰራጩት መረጃ #ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጠርጣሪው ሳይያዝ እንደ ተያዘ አድርጎ መረጃ ማሰራጨት ተገቢ እንዳልሆነ የገለፀው የአዲስ አበባ…
" እስካሁን ፍትሕ አልተሰጠም "

በአዲስ አበባ ፣ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 14 ' አስኮ አዲስ ሰፈር ' በጥይት ተመተው የተገደሉት የበድር መስጂድ ኢማምና ኸጢብ እንዲሁም በመስጂዱ የተለያዩ ኪታቦችን በማቅራት የሚታወቁት አቅሪ ሸይኽ አብዱ ያሲን ከተገደሉ ዛሬ 20 ቀን ሆኗል። 

ሸይኽ አብዱ የተገደሉት ከዒሻ ሰላት በኃላ ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በጥይት ተመተው እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።

ምንም እንኳን ሼይኽ አብዱ ከተገደሉ በርካታ ቀናት ቢያልፍም እስካሁን #ፍትህ እንዳልተሰጠ ፤ ይህም በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ሃዘን እንደፈጠረ " ሃሩን ሚዲያ " ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ በሼይኽ አብዱ ያሲን ግድያ ይጠረጠራል ያለው " መሀመድ ሽኩር አበባው " የተባለ ግለሰብ እንደነበር ይታወሳል።

ግለሰቡን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ መሆኑን ከመግለፅ ባለፈ በማህበራዊ ሚዲያ ፎቶውን በማሰራጨት ህብረተሰቡ ያለበትን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቦም ነበር።

ከዛ በኃላ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ / ስለመገኘቱ ምንም የተባለ ነገር የለም።

@tikvahethiopia
😭1.31K120😢94😡88🙏56🕊27👏24😱22🥰20