TIKVAH-ETHIOPIA
የ2005 የ20/80 ባለ3 መኝታ ተመዝቢዎች ፦ " ... በ14ኛው ዙር የዕጣ አወጣጥ የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች በቴክኖሎጂ ሆነ በማኑዋል ዕጣ የማውጣት ሂደቶች በሚፈጠሩ ችግሮች ሊወጣለት ከሚገባው ባለእድለኛ ወጪ ለሌላ ለማይመለከተው አካል እንዳይተላለፉ የሄደበትን ርቀት እናደንቃለን፡፡ ነገር ግን ይህ ቁርጠኝነት በባለ3 መኝታ 2005 ዓ.ም የ20/80 ተመዝቢዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲገለጽ እንፈልጋለን፡፡…
#መልስ_ያላገኘው_ጥያቄ
የ2005 የ20/80 የባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤት ቆጣቢዎች ባለፈው ሙሉ በሙሉ የተሰረዘው ዕጣ ሳይወጣ የእነሱ ጉዳይ ላይ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ግልፅ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው በድጋሚ አሳሰቡ።
የጋራ መኖሪያ ቤት ይደርሰናል ብለው እየቆጠቡ ያሉ ወገኖች አለን ስላሏቸው ጥያቄዎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማሳወቃችን አይዘነጋም።
" ዛሬም ድረስ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ የሚሰጠን አጥተናል " ያሉት ነዋሪዎቹ " ከልጆቻችን ምግብ ቀንሰን፣ በቤት ክራይ እየተሰቃየንና እየተማረርን ላለፉት 9 ዓመታት ቆጥበን ስለምን በዕጣው ልንካተት እንዳልቻልን በግልፅ ሊነገረን ይገባል " ብለዋል።
የቀጣዩ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ከመውጣቱ በፊትም መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል።
የ2005 ዓ/ም 20/80 ለባለ 3 መኝታ ቆጣቢዎቹ ፤ " #ቤቶቹ_የትገቡ ? ፣ #ተስፋ_አድርገን_ነበር ፤ #13ኛው_ዙር_ላይ_97_አልቋል_ብላችሁን_አልነበር?! ፤ #ባለ3_መኝታ_ኦዲት_ይደረግ ፤ #ፍትህ_እንሻለን! "በሚሉ እና በሌሎች ሀሽታጎች በተለይም በማህበራዊ ሚዲያ በመሰባሰብ ጥያቄያቸው መልስ እንዲያገኝ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን ገልፀዋል።
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72439?single
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72244?single
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72384?single
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72271
@tikvahethiopia
የ2005 የ20/80 የባለ 3 መኝታ የጋራ መኖሪያ ቤት ቆጣቢዎች ባለፈው ሙሉ በሙሉ የተሰረዘው ዕጣ ሳይወጣ የእነሱ ጉዳይ ላይ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ግልፅ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው በድጋሚ አሳሰቡ።
የጋራ መኖሪያ ቤት ይደርሰናል ብለው እየቆጠቡ ያሉ ወገኖች አለን ስላሏቸው ጥያቄዎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማሳወቃችን አይዘነጋም።
" ዛሬም ድረስ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ የሚሰጠን አጥተናል " ያሉት ነዋሪዎቹ " ከልጆቻችን ምግብ ቀንሰን፣ በቤት ክራይ እየተሰቃየንና እየተማረርን ላለፉት 9 ዓመታት ቆጥበን ስለምን በዕጣው ልንካተት እንዳልቻልን በግልፅ ሊነገረን ይገባል " ብለዋል።
የቀጣዩ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ከመውጣቱ በፊትም መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል።
የ2005 ዓ/ም 20/80 ለባለ 3 መኝታ ቆጣቢዎቹ ፤ " #ቤቶቹ_የትገቡ ? ፣ #ተስፋ_አድርገን_ነበር ፤ #13ኛው_ዙር_ላይ_97_አልቋል_ብላችሁን_አልነበር?! ፤ #ባለ3_መኝታ_ኦዲት_ይደረግ ፤ #ፍትህ_እንሻለን! "በሚሉ እና በሌሎች ሀሽታጎች በተለይም በማህበራዊ ሚዲያ በመሰባሰብ ጥያቄያቸው መልስ እንዲያገኝ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን ገልፀዋል።
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72439?single
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72244?single
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72384?single
https://tttttt.me/tikvahethiopia/72271
@tikvahethiopia
👍455👏34😢18🙏17🥰8❤5
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይፈለጋል #Wanted ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል። አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠርጠሪው እንደተያዘ በማስመሰል የሚያሰራጩት መረጃ #ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጠርጣሪው ሳይያዝ እንደ ተያዘ አድርጎ መረጃ ማሰራጨት ተገቢ እንዳልሆነ የገለፀው የአዲስ አበባ…
" እስካሁን ፍትሕ አልተሰጠም "
በአዲስ አበባ ፣ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 14 ' አስኮ አዲስ ሰፈር ' በጥይት ተመተው የተገደሉት የበድር መስጂድ ኢማምና ኸጢብ እንዲሁም በመስጂዱ የተለያዩ ኪታቦችን በማቅራት የሚታወቁት አቅሪ ሸይኽ አብዱ ያሲን ከተገደሉ ዛሬ 20 ቀን ሆኗል።
ሸይኽ አብዱ የተገደሉት ከዒሻ ሰላት በኃላ ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በጥይት ተመተው እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።
ምንም እንኳን ሼይኽ አብዱ ከተገደሉ በርካታ ቀናት ቢያልፍም እስካሁን #ፍትህ እንዳልተሰጠ ፤ ይህም በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ሃዘን እንደፈጠረ " ሃሩን ሚዲያ " ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ በሼይኽ አብዱ ያሲን ግድያ ይጠረጠራል ያለው " መሀመድ ሽኩር አበባው " የተባለ ግለሰብ እንደነበር ይታወሳል።
ግለሰቡን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ መሆኑን ከመግለፅ ባለፈ በማህበራዊ ሚዲያ ፎቶውን በማሰራጨት ህብረተሰቡ ያለበትን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቦም ነበር።
ከዛ በኃላ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ / ስለመገኘቱ ምንም የተባለ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ፣ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 14 ' አስኮ አዲስ ሰፈር ' በጥይት ተመተው የተገደሉት የበድር መስጂድ ኢማምና ኸጢብ እንዲሁም በመስጂዱ የተለያዩ ኪታቦችን በማቅራት የሚታወቁት አቅሪ ሸይኽ አብዱ ያሲን ከተገደሉ ዛሬ 20 ቀን ሆኗል።
ሸይኽ አብዱ የተገደሉት ከዒሻ ሰላት በኃላ ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በጥይት ተመተው እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።
ምንም እንኳን ሼይኽ አብዱ ከተገደሉ በርካታ ቀናት ቢያልፍም እስካሁን #ፍትህ እንዳልተሰጠ ፤ ይህም በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ሃዘን እንደፈጠረ " ሃሩን ሚዲያ " ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ በሼይኽ አብዱ ያሲን ግድያ ይጠረጠራል ያለው " መሀመድ ሽኩር አበባው " የተባለ ግለሰብ እንደነበር ይታወሳል።
ግለሰቡን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ መሆኑን ከመግለፅ ባለፈ በማህበራዊ ሚዲያ ፎቶውን በማሰራጨት ህብረተሰቡ ያለበትን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቦም ነበር።
ከዛ በኃላ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ / ስለመገኘቱ ምንም የተባለ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
😭1.31K❤120😢94😡88🙏56🕊27👏24😱22🥰20