TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somali #Afar #ሰላም #ውይይት

ትላንት የአፋርና የሱማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ኮንፈረንስ በአዳማ ተካሂዶ ነበር።

የሰላም ኮንፈረንሱ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት ዓላማ ያደረገ ነው መሆኑን ሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።

በአካባቢዎቹ የሚታዩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ሰላምን ለማምጣት ወደ ግጭት ለሚያመሩ ጉዳዮችም መፍትሔዎች ተለይተው የተቀመጡበት መድረክ ነው ተብሏል።

የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ፤ በግጭት ምክንያት ከኖሩበት ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው እየኖሩ ችግሮችን እየተጋፈጡ ያሉ ወገኖች ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ሊደረጉ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም በመድረኩ መነሳቱን ከሰላም ሚኒስቴር በኩል የወጣው መረጃ ያሳያል።

ባለፈው ዓመት በተነሳ ግጭት ከዘጠኝ ወር በላይ ቤታቸው ተፈናውለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በየዘመዶቻቸው ቤት የተጠለሉ በርካታ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
👍2🙏1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somali

የሶማሌ ክልል ፀጥታ ቢሮ ፤ ከሰሞኑን በጅግጅጋ ኤርፖርት በፀጥታ ኃይል ከተገደሉት ጄዌሪያ መሀመድ ጋር በተያያዘ ህዝቡን እና ከተማውን ለማበጣበጥ ፣ ሁከት እና ግርግር ለመፍጠር እንዲሁም ሌብነትና ዘረፋ ለመፈፀም ፍላጎት ያላቸው አካላት መኖራቸውን ጠቁሞ ህዝቡ እነዚህን አካላት አይሆንም ሊላቸው/ሊገስፃቸው እንደሚገባ መንግስት ግን እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

ቢሮው የጄዌሪያን መሀመድ መገደልን ተከትሎ የተለያየ አይነት ስሜትና ፍላጎት ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ይስተዋላሉ ብሏል።

አንደኛ፦

በድርጊቱ በጣም ያዘኑ እና ሀዘናቸውንም በአግባቡ መግለፅ የሚፈልጉ ፍትህ እንዲገኝ የሚጠይቁ ናቸው።

ሁለተኛ፦

በዚህ የሀዘን ድባብና ክፉ ድርጊት ጥቅማቸውን የሚፈልጉ ሁከት እና ግርግር እንዲባባስ የሚፈልጉ በዚህ አጀንዳ ተሸጋግረው ሌላ ጥቅም የሚፈልጉ ናቸው።

ሶስተኛ፦

ፖለቲካዊ ፍላጎት ባይኖረውም ግን የሌብነት፣ ዘረፋ እና ብጥብጥን በውስጡ የያዘ ነው፤ ቢሮው፤ እንደዚህ አይነት ፍላጎት ያላቸው አካላት በዚህ አይነት ምክንያት ሌላው ላይ ተፅእኖ በመፍጠር ትላንት በባለፈው ስርዓት ጊዜ እንዳደረጉት ህዝብና ከተማን መበጥበጥ እና መዝረፍ የሚሹ አካላት የሚታወቁና ያልተደበቁ ናቸው ብሏል።

ትላንት የደረሰው ግፍና ተፅእኖ፣ መከራ እና ችግር ከግምት በማስገባት መንግስት የሚያደርገውን ትዕግስት ወደ ጎን በማየት በዚህ አይነት ተልዕኮ የሚሰማሩትን ህዝቡ የትላንቱን አይነት ጥፋት መድገም የለባችሁም በማለት ሊገስፃቸውና አይሆንም ሊላቸው ይገባል ብሏል ቢሮው።

ለክልሉ ህዝቦች አብሮነት ማይጠቅም፤ የነበረውን አንድነትና ህብረት የሚያበላሽ አይነት ፍላጎት ለ2ኛ ጊዜ እንዲመለስ መንግስት አይፈቅድም ያለው የፀጥታው ቢሮ እንዲህ አይነት አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል ብሏል።

@tikvahethiopia
👍633👎31🕊18😢1711🙏3
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Afar #Somali🚨

" የግጭቱ ማገርሸት ለሰላማዊ ሰዎች ግድያ እና መፈናቀል ምክንያት ሆኗል " - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋር እና ሶማሌ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት ማገርሸቱ ገልጿል።

ኮሚሽሙ ግጭቱ እንዳሳሰበውም አመልክቷል።

ኢሰመኮ በቅርቡ በሚያዚያ ወር የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ በሶማሊ ክልል ሽንሌ ዞን እና አፋር ክልል አዋሳኝ ያገረሸው ግጭት አሳሳቢ ነው ብሏል።

ግጭቱ ለሰላማዊ ሰዎች ግድያ እና መፈናቀል ምክንያት እንዳሆነ ገልጿል።

በኮሚሽኑ የጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ሰኢድ ደመቀ ለዶይቼ ቬለ በሰጡት ቃል ፤ " የአሁኑ ግጭት የተጀመረው ከግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም 2024 ወዲህ ነው " ብለዋል።

" በግጭቱ የተወሰኑ ሰዎች ሞት፤ መፈናቀል እና የአካል ጉዳት፤ የንብረት መውደም እንደደረሰ ነው ያለው መረጃ በእኛ በኩል ግጭቱ እንዳገረሸ። በትክልል ስንት ሰው ሞተ፤ ቆሰለ የሚለውን ገና በምርመራ የምናጣራው ነው " ብለዋል።

" በአሁኑ ወቅት ግን ጠቅለል ባለ መልኩ የሰው መፈናቀል፤ ሞት እና ጉዳት እንዳለ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ኢሰመኮ ከሁለቱ ክልሎች የመንግስት አስተዳዳሪዎች ተረዳሁት ባለው መሠረት ፥ በሁለቱም ክልሎች በኩል የሰላማዊ ሰዎች ግድያ እና መፈናቀሎች ተፈጽሟል።

በቅርቡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለተገኘው አዎንታዊ የሰላም ማስፈን ሂደት ሁለቱ ክልሎች ያሰጡትን አዎንታዊ ምላሽ ያደነቀው ኢሰመኮ፤ የተጀመረው የሰላም ጥረት እንዲቀጥል የፌዴራልም ሆነ የሁለቱ ክልሎች መንግስታት የቀጠለውን ግጭት እንዲያስቆሙት ጥሪውን አቅርቧል።

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የፌዴራል መንግስት አስቸኳይ የግጭት ማስቆም ጥረት እንዲያስደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

የሁለቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በቀጣይ ሕዝበ ሙስሊሙ ከሚያከብረው የኢድ አል-አደሃ በዓል አስቀድሞ ሰላም እንዲሰፍን ጥረት እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።

#DWAmharic #EHRC

@tikvahethiopia
271😭121🕊60😢28😡28🙏27😱11🤔9👏8
#Afar #Somali #Iftar

ዛሬ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች የኢፍጣር መርሐ ግብር በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሃጂ አወል አርባ፣ የሰላም ሚንስትሩ አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ተገኝተዋል።

#SomaliRegionGovCommunication

@tikvahethiopia
1.12K😁211🕊55🙏31😡20👏19😭15😢3🥰2