TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" የማህበራዊ ሚዲያው ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ተደራሽነትን እና ፍጥነትን በመስጠት ለጥላቻ ንግግር ምቹ ሜዳ ሆኗል " - ቮልከር ተርክ

ነገ እሁድ ሰኔ 11 / June 18 የዓለም አቀፍ የጸረ-ጥላቻ ንግግር መከላከል ቀን ይከበራል።

ቀኑን አስመልክቶ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የጥላቻ ንግግርና አደገኛ መልዕክቶችን " ሰፊ ስርጭት " መከላከልን ጨምሮ ለመቆጣጠር የተቀናጀ ዓለም አቀፍ ጥረቶች እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ቀኑን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ቮልከር ተርክ ፦

" ትልቅ ግብዓት ያለው ጥረት ዓለምን ከመከራ ሊያጸዳው ይችላል።

የጥላቻ መስፋፋት መለያየትን ለመዝራት፣ ለማፍረስ እና ከትክክለኛ ጉዳዮች ለማዘናጋት በሚፈልጉ አካላት እንደሚሰራጭ እናውቃለን።

የማህበራዊ ሚዲያው በተለይም ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ተደራሽነትን እና ፍጥነትን በመስጠት ለጥላቻ ንግግር ምቹ ሜዳ ሆኗል።

ጥላቻ ትምክህተኝነትን ፣ አድልዎንና አመጽን ያነሳሳል፤ ዓለማችንን ከጥላቻ የሚያጸዳው ጥይት፣ ማብሪያ ማጥፊያ የለውም።ነገር ግን የታለሙ እርምጃዎች ላይ ቢሰራ የጥላቻ ንግግሮችን ስርጭት መገደብ እና የሚያሰራጩትን ተጠያቂ ማድረግ ይቻላል።

በተጨማሪ ኩባንያዎች የጥላቻ ንግግርን በተመለከተ ለሚሰሩት እና ላልሰሩ ነገር ተጠያቂ መሆን አለባቸው። ጥላቻን የሚያቋርጡ አውታረ መረቦችን መገንባት እና ድምጾችን ማጉላት አለብን። ለአብነትም የኃይማኖት መሪዎች ለጥላቻ እና ለአመጽ ማነሳሳት ምላሽ እንዲሰጡ ማድረግ አንዱ ነው።

በአለም አቀፍ ደረጃ በጋዜጠኞች እና በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ ያለአግባብ ጥቅም ላይ የሚውሉት ከጥላቻ ንግግር ጋር የተገናኙ ህጎች መስፋፋታቸውም የጥላቻ ንግግርን ከማስፋፋት ባልተናነሰ ጉዳት ያለው ነው። "

Credit : #አልአይን

@tikvahethiopia
👍610👎12067🕊10🥰9🙏8😢6😱4
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ?

- " ችግሩ የተከሰተው አንድ ሂሳብ ማስታረቅ ቅልጥፍና እንዲያመጣ ታስቦ የተሰራ የሲስተም ማሻሻያ ሲተገበር ስህተት በመፈጠሩ ነው። የተፈጠረው ስህተት ለሌቦች ቀዳዳ ከፍቶ ነበር። "

- " የሲስተም ማሻሻያው የተተገበረው አርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ ነበር። ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ችግር እንዳለ ሊለይ ችሏል። ይህን ተከትሎም አንዳንድ የተጠረጠሩ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ይህም ሆኖ ሙሉ በሙሉ ችግሩ ስላልቆመ ሁሉም የዲጂታል ባንክ ስርዓቶች እንዲቋረጡ ተደርጎ ነበር። "

- " ባንኩ ችግሩ በተከሰተበት ወቅት ከ490 ሺህ በላይ የገንዘብ ልውውጥ ተካሂዷን። ሌሊቱን ሙሉ ግብይት ሲፈጸምባቸው የነበረባቸው የባንክ ሂሳቦች በሙሉ እስኪጣራ ድረስ #እንዲታገድ ተደርጓል። "

- " በቀጣይ ከፍተኛ እና ያልተገባ ግብይት የፈጸሙ አካላትን እየለየን ለህግ የማቅረብ ስራ ይሰራል። "

- " የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በወንጀሉ ዋነኛ ተዋናይ መሆናቸው አሳዝኖናል። በየአካባቢው ያሉ የዲስትሪክት ኃፊዎች በየአካባው ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች የወሰዱትን ገንዘብ #እንዲመልሱ እየተደረገ ነው። "

- " ከተፈጠረው ችግር ጋር ተያይዞ አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው። የችግሩ መሰረታዊ መንስዔ እና ያስከተለውን ጉዳትም ምርመራው ሲጠናቀቅ ይፋ ይደረጋል። "

- " ባንኩ ላይ የደረሰው ጉዳት ባንኩ ካለው ሀበት እና አቅም አንጻር የጎላ ተጽእኖ የለውም፤ ከደንበኞች ሂሳብ ጋርም አይገናኝም። " #አልአይን

@tikvahethiopia
790😡459🤔123😭99👏64🙏64🕊45😢43🥰35😱25
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ትላንት ታጣቂዎች በሩስያ ፣ #ሞስኮ በሚገኘው የክሮከስ አዳራሽ የሙዚቃ ዝግጅት ለመታደም በተሰበሰቡ በርካታ ሰዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ የተገደሉ ሰዎች 115 የደረሱ ሲሆን 100 ሰዎች መቁሰላቸውን የሩሲያ የደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል። ከተገደሉት ውስጥ ህፃናትም እንደሚገኙበት ተነግሯል። 4 ታጣቂዎችን ጨምሮ 11 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሩስያ ባለስልጣናት አሳውቀዋል። የሩሲያ…
#ሩስያ

" ሽብርተኞችን የሚጠብቀው የበቀል እርምጃ ብቻ ነው " - ቭላድሚር ፑቲን

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከትላንትና የሽብር ጥቃት በኃላ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም ነገ መጋቢት 15 በመላው ሩሲያ የሀዘን ቀን እንደሚሆን ተናግረዋል። " የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ዜጎቻችን ይዘከሩበታል " ብለዋል።

አሁን ላይ በጥቃቱ ላይ ቀጥታ ተሳትፎ የነበራቸው ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጠር ስር መዋላቸውን ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፤ ሌላ የጅምላ ግድያ እንዳይፈጸም የጸጥታ ኃሎች ሰፊ ስራ እየሰሩ ነው ብለዋል።

" በትናንትናው የሽብር ጥቃት ላይ የተሳተፈ እና ያገዛቸው የትኛውም አካል ለህግ ይቅርባል " ሲሉ ዝተዋል።

ፕሬዜዳንቱ በትናንትናው የሽብር ጥቃት ላይ የተሳተፉ 4 ወንጀለኞች ወደ ዩክሬን ሊያመልጡ ሲሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል።

" አሁን ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት እንደሚያመላክተው በዩክሬን በኩል ሽብርተኞች ለማስመለጥ የሚያስችል መንገድ በድንበር በኩል ተዘጋጅቶ እንደነበረ ነው "  ብለዋል።

" ሩሲያ በዚህ የሽብር ጥቃት ላይ የተሳተፉ ሁሉንም አካላት ለይታ ትቀጣለች " ያሉት ፑቲን፤ " ሽብርተኞችን የሚጠብቀው የበቀል እርምጃ ብቻ ነው፤ ከዚህ ውጪ ምንም አማራጭ እና ተስፋ የላቸውም " ሲሉ ዝተዋል። #አልአይን

@tikvahethiopia
👏2.77K297🕊102🤔52🙏46😭43😡24😱21😢9