TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ፦ - ከኦነግ ሸኔ፣ - ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ - ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ - ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ - ወደ አዲስ…
#ፓርላማ
" እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ?
#አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?
" የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለ እርሶ እና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብቦት ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ አለፍ ሲል ተጠየቅ የቀረበቦት የወጡበትን ብሄር በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ ሲሰጡ የቅርብ ትዝታችን ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጥያቄ የማቀርብልዎ እኔ በብሄሬ አይደለም፤ ይህን ጥያቄ ሳቀርብልዎ እርሶ የሚወክሉትን ብሄር በመጥላት አይደለም ምላሽ እና ማብራሪያ ሲሰጡም ለጥያቄዬ ብሄርዎን እና ምናልባት የመንግስት ግልበጣ ሴራ ነው ከሚል ምላሽ እና ማብራሪያ እንዳይሰጡ ከወዲሁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ።
ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ ...
የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል።
... የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች በሪፖርቱ ያቀረበው ነው።
አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደህንነት እና የሀገር ልዑላዊነት ዋና ስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው እርሶ የሚመሩት መንግስትን ነው።
እርሶ በአፍዎ ኢትዮጵያ አትፈርስም ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው።
የበርካታ ሀገራት መሪዎች መሰል ኃላፊነትን በወጉ አለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀው ስልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል፤ በሀገራችንም የቀድሞ ጠ/ሚ ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ህዝባዊ ተጠየቅነት ሲቀርብባቸው ስልጣን መልቀቃቸውን እናስታውሳለን እርስዎም ወደ ስልጣን የመጡት በዚሁ ተጠየቅ ምክንያት ነው፤ እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? አመሰግናለሁ !! "
@tikvahethiopia
" እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ?
#አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?
" የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለ እርሶ እና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብቦት ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ አለፍ ሲል ተጠየቅ የቀረበቦት የወጡበትን ብሄር በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ ሲሰጡ የቅርብ ትዝታችን ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጥያቄ የማቀርብልዎ እኔ በብሄሬ አይደለም፤ ይህን ጥያቄ ሳቀርብልዎ እርሶ የሚወክሉትን ብሄር በመጥላት አይደለም ምላሽ እና ማብራሪያ ሲሰጡም ለጥያቄዬ ብሄርዎን እና ምናልባት የመንግስት ግልበጣ ሴራ ነው ከሚል ምላሽ እና ማብራሪያ እንዳይሰጡ ከወዲሁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ።
ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ ...
የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል።
... የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች በሪፖርቱ ያቀረበው ነው።
አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደህንነት እና የሀገር ልዑላዊነት ዋና ስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው እርሶ የሚመሩት መንግስትን ነው።
እርሶ በአፍዎ ኢትዮጵያ አትፈርስም ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው።
የበርካታ ሀገራት መሪዎች መሰል ኃላፊነትን በወጉ አለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀው ስልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል፤ በሀገራችንም የቀድሞ ጠ/ሚ ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ህዝባዊ ተጠየቅነት ሲቀርብባቸው ስልጣን መልቀቃቸውን እናስታውሳለን እርስዎም ወደ ስልጣን የመጡት በዚሁ ተጠየቅ ምክንያት ነው፤ እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? አመሰግናለሁ !! "
@tikvahethiopia
❤8.31K👍1.26K👎610🙏271😱98🥰78🕊73🤔56😢34