#ፊቼ_ጨምበላላ
የሲዳማ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምባላላ በዓል እየተከበረ ይገኛል።
ዛሬ በዓሉ በሲምፖዚየምና ሌሎች ዝግጅቶች በሀዋሳ ተከብሯል።
በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ የፊቼ ጫምባላላ ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርቧል።
በዛሬው የበዓሉ ዋዜማ የ ”ሻፌታ” ሥነ-ሥርዓትን ጨምሮ ሌሎችም ዝግጅቶች ነበሩ።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳና የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎና የዞን አመራሮች ተገኝተው ነበር።
በተጨማሪ የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ፣ አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤና አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ታድመው እንደነበር ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
የሲዳማ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምባላላ በዓል እየተከበረ ይገኛል።
ዛሬ በዓሉ በሲምፖዚየምና ሌሎች ዝግጅቶች በሀዋሳ ተከብሯል።
በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ የፊቼ ጫምባላላ ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርቧል።
በዛሬው የበዓሉ ዋዜማ የ ”ሻፌታ” ሥነ-ሥርዓትን ጨምሮ ሌሎችም ዝግጅቶች ነበሩ።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳና የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎና የዞን አመራሮች ተገኝተው ነበር።
በተጨማሪ የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ፣ አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤና አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ታድመው እንደነበር ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
👍1