TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ፊቼ_ጨምበላላ

የሲዳማ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምባላላ በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ዛሬ በዓሉ በሲምፖዚየምና ሌሎች ዝግጅቶች በሀዋሳ ተከብሯል።

በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ የፊቼ ጫምባላላ ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርቧል።

በዛሬው የበዓሉ ዋዜማ  የ ”ሻፌታ” ሥነ-ሥርዓትን ጨምሮ ሌሎችም  ዝግጅቶች  ነበሩ።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳና የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎና የዞን አመራሮች ተገኝተው ነበር።

በተጨማሪ የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ፣ አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤና አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ታድመው እንደነበር ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
👍1