TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Iftar

ዛሬና ትላንት ቅዳሜ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።

ዛሬ በአፋር ክልል መዲና ሰመራ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት የተካሄደ ሲሆን በጅማ ከተማም እጅግ ከፍተኛ የሰው ቁጥር የተገኘበት የኢፍጣር ስነሥርዓት ታካሂዷል።

በተመሳሳይ ዛሬ በአጋሮ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዳል።

ትላንት በአፋር ኤሊደአር ፣ ስልጤ ዞን ቃዋቅቶ እና በቂልጦ ከተማ፣ ሰሜን ምዕራብ ሸዋ ጎሮ ወረዳ፣ በአርሲ ነጌሌ፣ ባሌጎባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።

በሌላ መረጃ ፥ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 18 በአዳማ ከተማ፣ ረቡዕ ሚያዚያ 19 ደግሞ በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት እንደሚካሄድ ታውቋል።

በተጨማሪ ከጥቂት ቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚካሄደው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

ፎቶዎች ፦ telegra.ph/Iftar-04-24

@tikvahethiopia
👍158👎6623😢1
#Afar #Somali #Iftar

ዛሬ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች የኢፍጣር መርሐ ግብር በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሃጂ አወል አርባ፣ የሰላም ሚንስትሩ አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ተገኝተዋል።

#SomaliRegionGovCommunication

@tikvahethiopia
1.12K😁211🕊55🙏31😡20👏19😭15😢3🥰2