TIKVAH-ETHIOPIA
#Iftar የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ነው። አርብ በደሴ ለሁለተኛ ጊዜ ታላቅ የሆነ የጎዳና ላይ ኢፍጧር መካሄዱ ይታወሳል። ትላንት ደግሞ በቡታጅራ ለመጀመሪያ ጊዜ ታላቅ ኢፍጧር ከማርስ ታወር ህንፃ - መናኸሪያ ድረስ ተካሂዷል (ፎቶው ከላይ ተያይዟል) ። ዝግጅቱን ያዘጋጀው ኢኽላስ በጎ አድራጎት ማህበር መሆኑን አዘጋጆቹ ገልፀውልናል። በአሁን ሰዓት ደግሞ በኮምቦልቻ…
#Iftar
#Assosa #Kombolcha #AA #Harar #Metu #Tullubolo
ዛሬ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ላይ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጧር ስነስርዓት ተካሂዷል።
በተለይም በታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ሀረር ከተማ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምዕመን በተገኘበት ነው የአፍጥር ስነ ስርኣቱ የተካሄደው።
በኮምቦልቻ ከተማ ፥ ዛሬ ሁለተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር " ኑ አብረን እናፍጥር " በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል። በስነስርዓቱ ላይ ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ባለፈ የሌሎች እምነት ተከታዮች የተገኙ ሲሆን ስነስርኣቱ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቋል።
በመዲናችን አዲስ አበባ ደግሞ በነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት አስተባባሪነት ዛሬ በ11 ጎዳናዎች ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዶ በሰላም መጠናቀቁን አዘጋጆች አሳውቀውናል።
በተጨማሪ ዛሬ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ከተካሄደባቸው ከተሞች መካከል አሶሳ አንዷ ስትሆን ፤ ስነ ስርዓቱ በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች አስተባባሪነት ነው የተካሄደው። በመርሃ ግብሩ ላይ ወላጅ አልባ እና አቅመ ደካሞች፣ አረጋዊያን እና ደጋፊ የሌላቸው ወገኖች ከከተማው ሙስሊም ህብረተሰብ ጋር በጋራ አፍጥረዋል።
በአፋር ክልል ዱብቲ ከተማም ታላቅ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል ፤ " አንድነታችንን እያጠናከርን ኑ በጋራ እናፍጥር " በሚል መሪ ሀሳብ ነው የተካሄደው።
በመቱ እና በቱሉቦሎም ዛሬ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።
@tikvahethiopia
#Assosa #Kombolcha #AA #Harar #Metu #Tullubolo
ዛሬ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ላይ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጧር ስነስርዓት ተካሂዷል።
በተለይም በታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ሀረር ከተማ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምዕመን በተገኘበት ነው የአፍጥር ስነ ስርኣቱ የተካሄደው።
በኮምቦልቻ ከተማ ፥ ዛሬ ሁለተኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር " ኑ አብረን እናፍጥር " በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል። በስነስርዓቱ ላይ ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ባለፈ የሌሎች እምነት ተከታዮች የተገኙ ሲሆን ስነስርኣቱ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቋል።
በመዲናችን አዲስ አበባ ደግሞ በነሲሓ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት አስተባባሪነት ዛሬ በ11 ጎዳናዎች ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዶ በሰላም መጠናቀቁን አዘጋጆች አሳውቀውናል።
በተጨማሪ ዛሬ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ከተካሄደባቸው ከተሞች መካከል አሶሳ አንዷ ስትሆን ፤ ስነ ስርዓቱ በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች አስተባባሪነት ነው የተካሄደው። በመርሃ ግብሩ ላይ ወላጅ አልባ እና አቅመ ደካሞች፣ አረጋዊያን እና ደጋፊ የሌላቸው ወገኖች ከከተማው ሙስሊም ህብረተሰብ ጋር በጋራ አፍጥረዋል።
በአፋር ክልል ዱብቲ ከተማም ታላቅ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል ፤ " አንድነታችንን እያጠናከርን ኑ በጋራ እናፍጥር " በሚል መሪ ሀሳብ ነው የተካሄደው።
በመቱ እና በቱሉቦሎም ዛሬ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።
@tikvahethiopia
👍1.02K❤186👎105👏50🥰27😱14😢14
#IFTAR
ዛሬ እና ትላንት በተለያዩ ከተሞች ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት ታካሂዷል።
የኢፍጣር ስነስርዓት ከተካሄደባቸው ከተሞች አንዷ መዲናችን አዲስ አበባ ስትሆን በቤተል አደባባይ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።
በደ/ወሎ ልጓማ ከተማ፣ ሶማሌ ክልል ቀብሪደሃር ከተማ ፣ በወራቤ ከተማ ፣ በአፋር ማንዳ ከተማ ፣ በስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ ፤ ኬራቴ ከተማ ፣ ሻሸመኔ ከተማ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።
ትላንት ደግሞ ፤ በለገጣፎ ለገዳዲ ፣ በጅማ ዞን ኦማንዳ ወረዳ ፣ በኢሊአባቦር ዞን አልጌ ሰቺ ወረዳ ፣ ሰንዳፋ በኬ ፣ ቡራዩ ፣ ቢሾፍቱ ከተማ ፣ ጅማ ዞን ዴዶ ወረዳ፣ በወልቃይት ሁመራ እና በወልቂጤ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።
የሁሉንም የጎዳና ላይ ኢፍጣር ፎቶዎች ይመልከቱ ፦ https://telegra.ph/Iftar-04-22
@tikvahethiopia
ዛሬ እና ትላንት በተለያዩ ከተሞች ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት ታካሂዷል።
የኢፍጣር ስነስርዓት ከተካሄደባቸው ከተሞች አንዷ መዲናችን አዲስ አበባ ስትሆን በቤተል አደባባይ ታላቅ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።
በደ/ወሎ ልጓማ ከተማ፣ ሶማሌ ክልል ቀብሪደሃር ከተማ ፣ በወራቤ ከተማ ፣ በአፋር ማንዳ ከተማ ፣ በስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ ፤ ኬራቴ ከተማ ፣ ሻሸመኔ ከተማ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።
ትላንት ደግሞ ፤ በለገጣፎ ለገዳዲ ፣ በጅማ ዞን ኦማንዳ ወረዳ ፣ በኢሊአባቦር ዞን አልጌ ሰቺ ወረዳ ፣ ሰንዳፋ በኬ ፣ ቡራዩ ፣ ቢሾፍቱ ከተማ ፣ ጅማ ዞን ዴዶ ወረዳ፣ በወልቃይት ሁመራ እና በወልቂጤ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።
የሁሉንም የጎዳና ላይ ኢፍጣር ፎቶዎች ይመልከቱ ፦ https://telegra.ph/Iftar-04-22
@tikvahethiopia
👍453👎136❤44🥰33👏19😢3
#Iftar
ዛሬና ትላንት ቅዳሜ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።
ዛሬ በአፋር ክልል መዲና ሰመራ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት የተካሄደ ሲሆን በጅማ ከተማም እጅግ ከፍተኛ የሰው ቁጥር የተገኘበት የኢፍጣር ስነሥርዓት ታካሂዷል።
በተመሳሳይ ዛሬ በአጋሮ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዳል።
ትላንት በአፋር ኤሊደአር ፣ ስልጤ ዞን ቃዋቅቶ እና በቂልጦ ከተማ፣ ሰሜን ምዕራብ ሸዋ ጎሮ ወረዳ፣ በአርሲ ነጌሌ፣ ባሌጎባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።
በሌላ መረጃ ፥ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 18 በአዳማ ከተማ፣ ረቡዕ ሚያዚያ 19 ደግሞ በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት እንደሚካሄድ ታውቋል።
በተጨማሪ ከጥቂት ቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚካሄደው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
ፎቶዎች ፦ telegra.ph/Iftar-04-24
@tikvahethiopia
ዛሬና ትላንት ቅዳሜ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዷል።
ዛሬ በአፋር ክልል መዲና ሰመራ ከተማ ታላቅ የጎዳና ላይ የኢፍጣር ስነስርዓት የተካሄደ ሲሆን በጅማ ከተማም እጅግ ከፍተኛ የሰው ቁጥር የተገኘበት የኢፍጣር ስነሥርዓት ታካሂዷል።
በተመሳሳይ ዛሬ በአጋሮ የኢፍጣር ስነስርዓት ተካሂዳል።
ትላንት በአፋር ኤሊደአር ፣ ስልጤ ዞን ቃዋቅቶ እና በቂልጦ ከተማ፣ ሰሜን ምዕራብ ሸዋ ጎሮ ወረዳ፣ በአርሲ ነጌሌ፣ ባሌጎባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሂዷል።
በሌላ መረጃ ፥ የፊታችን ማክሰኞ ሚያዚያ 18 በአዳማ ከተማ፣ ረቡዕ ሚያዚያ 19 ደግሞ በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት እንደሚካሄድ ታውቋል።
በተጨማሪ ከጥቂት ቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚካሄደው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
ፎቶዎች ፦ telegra.ph/Iftar-04-24
@tikvahethiopia
👍158👎66❤23😢1
#Afar #Somali #Iftar
ዛሬ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች የኢፍጣር መርሐ ግብር በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሃጂ አወል አርባ፣ የሰላም ሚንስትሩ አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ተገኝተዋል።
#SomaliRegionGovCommunication
@tikvahethiopia
ዛሬ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች የኢፍጣር መርሐ ግብር በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሃጂ አወል አርባ፣ የሰላም ሚንስትሩ አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ተገኝተዋል።
#SomaliRegionGovCommunication
@tikvahethiopia
❤1.12K😁211🕊55🙏31😡20👏19😭15😢3🥰2