#SNNPRS
የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል መግለጫ አውጥቷል።
የክልሉ መንግስት በመግለጫው ትላንት ሚያዝያ 20/2014 ዓ/ም በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ እና በሳንኩራ ወረዳ ላይ በሀይማኖት ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።
የተፈፀመው ጥቃት ለዘመናት ተቻችለው እና ተከባብረው በኖሩ የልዩ ልዩ እምነት ተከታይ ህዝቦች ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብሏል።
" ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ በጽንፈኛ ሀይሎች የሚደርሰውን ጥቃት አልታገስም " ያለው የክልሉ መንግስት በስልጤ ዞን የተጀመረው ጥቃት ወደ ሌሎች የክልሉ አካባቢዎች እንዳይዛመት ሰላም ወዳዱ የክልሉ ህዝብ ከመንግስት ጎን በመሆን የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ ይኖርበታል ብሏል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይያዟል)
@tikvahethiopia
የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል መግለጫ አውጥቷል።
የክልሉ መንግስት በመግለጫው ትላንት ሚያዝያ 20/2014 ዓ/ም በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ እና በሳንኩራ ወረዳ ላይ በሀይማኖት ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።
የተፈፀመው ጥቃት ለዘመናት ተቻችለው እና ተከባብረው በኖሩ የልዩ ልዩ እምነት ተከታይ ህዝቦች ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብሏል።
" ሀይማኖትን ሽፋን በማድረግ በጽንፈኛ ሀይሎች የሚደርሰውን ጥቃት አልታገስም " ያለው የክልሉ መንግስት በስልጤ ዞን የተጀመረው ጥቃት ወደ ሌሎች የክልሉ አካባቢዎች እንዳይዛመት ሰላም ወዳዱ የክልሉ ህዝብ ከመንግስት ጎን በመሆን የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ ይኖርበታል ብሏል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይያዟል)
@tikvahethiopia
👍2❤1👎1
#SNNPRS
አንደኛ በመኸር ዝናብ መዛበት ሁለተኛ በግጭት ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰዎች መጨመር በደቡብ ክልል የተረጂዎችን ቁጥር ጨምሯል።
የደቡብ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እንደሚለው፤ አሁን ላይ በደቡብ ክልል 3.3 ሚሊዮን ሰዎች ለከፋ ረሃብ / የምግብ ዋስትና ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ ሲል ተንብዩዋል።
የከፋ ለሆነ የምግብ ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ የተባሉት ከዚህ ቀደም የምግብ ችግር ኖሮባቸው በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ሲደገፉ የነበሩ (917 ሺህ)፣ በግጭት የተፈናቀሉ (122 ሺ) ፣ በመኸር ዝናብ መጥፋት ምርት ያላገኙ (2.3 ሚሊዮን) ነዋሪዎች ናቸው።
በደቡብ ክልል የከፋ የምግብ እጦት ካለባቸው አካባቢዎች አንዱ የኮንሶ ዞን ህፃናት እና እናቶች ለከፋ ጉዳት መዳረጋቸውን ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው።
በዞኑ አብዛኛው አካባቢዎች የእርዳታ አቅርቦት እየደረሰ እንዳለሆነ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።
አንድ የኮልሜ ክላስተር ነዋሪ ፦
" ምንም አይነት እየመጣ አይደለም። ምንም አይነት ድጋፍ አላገኘንም። እኛ መጠበቅ ካለብን መንግሥት እንዲደርስልን ነው። ከሞት እንዲታደገን ነው። በገንዘብም ቢሆን መንግሥት እንዲረዳንና ከዚህ ዓመት ቢያሻግረን ብለን ነው የምንማፀነው። "
ሌላ ነዋሪ ፦
" አንደኛ ዝናብ ጠፋ ፣ በዛ ላይ የከብት ሳርም የለም። በመንግስት በኩል የሚደረግ እርዳታም የለም " ብለዋል።
የኮንሶ ዞን የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ከፈኔ ቲጫኖ በዞኑ ካላት ተረጂዎች እስካሁን ድጋፍ ያገኙ ግማሽ እንኳን እንደማይሆኑ ተናግረዋል።
በተለይ ደግሞ ከሀምሌ ወር ጀምሮ የምግብ ድጋፍ ፈላጊው ሊጨምር እንደሚችል ገልፀዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/SNNPRS-07-21
#ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
አንደኛ በመኸር ዝናብ መዛበት ሁለተኛ በግጭት ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰዎች መጨመር በደቡብ ክልል የተረጂዎችን ቁጥር ጨምሯል።
የደቡብ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እንደሚለው፤ አሁን ላይ በደቡብ ክልል 3.3 ሚሊዮን ሰዎች ለከፋ ረሃብ / የምግብ ዋስትና ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ ሲል ተንብዩዋል።
የከፋ ለሆነ የምግብ ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ የተባሉት ከዚህ ቀደም የምግብ ችግር ኖሮባቸው በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ሲደገፉ የነበሩ (917 ሺህ)፣ በግጭት የተፈናቀሉ (122 ሺ) ፣ በመኸር ዝናብ መጥፋት ምርት ያላገኙ (2.3 ሚሊዮን) ነዋሪዎች ናቸው።
በደቡብ ክልል የከፋ የምግብ እጦት ካለባቸው አካባቢዎች አንዱ የኮንሶ ዞን ህፃናት እና እናቶች ለከፋ ጉዳት መዳረጋቸውን ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው።
በዞኑ አብዛኛው አካባቢዎች የእርዳታ አቅርቦት እየደረሰ እንዳለሆነ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።
አንድ የኮልሜ ክላስተር ነዋሪ ፦
" ምንም አይነት እየመጣ አይደለም። ምንም አይነት ድጋፍ አላገኘንም። እኛ መጠበቅ ካለብን መንግሥት እንዲደርስልን ነው። ከሞት እንዲታደገን ነው። በገንዘብም ቢሆን መንግሥት እንዲረዳንና ከዚህ ዓመት ቢያሻግረን ብለን ነው የምንማፀነው። "
ሌላ ነዋሪ ፦
" አንደኛ ዝናብ ጠፋ ፣ በዛ ላይ የከብት ሳርም የለም። በመንግስት በኩል የሚደረግ እርዳታም የለም " ብለዋል።
የኮንሶ ዞን የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ከፈኔ ቲጫኖ በዞኑ ካላት ተረጂዎች እስካሁን ድጋፍ ያገኙ ግማሽ እንኳን እንደማይሆኑ ተናግረዋል።
በተለይ ደግሞ ከሀምሌ ወር ጀምሮ የምግብ ድጋፍ ፈላጊው ሊጨምር እንደሚችል ገልፀዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/SNNPRS-07-21
#ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
👍48😢43❤8🙏7🥰4
#SNNPRS #GurageZone
" ሰዎች ለምን የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ በሚል እየታሰሩ ናቸው " - ነዋሪዎች
" ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር ውለዋል " - የደቡብ ክልል ፖሊስ
በደቡብ ክልላዊ መንግስት ጉራጌ ዞን ከክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች እየተሰሩ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
እየታሰሩ ከሚገኙት መካከል በዞኑ በኃላፊነት ቦታ ያሉ ጭምር መሆናቸው ተጠቁሟል።
ትላንት ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ አቶ በላቸው ገብረማርያን የተባሉ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ የዞኑ ነዋሪ ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ 13 ሰዎች እንደታሰሩ ከነዚህ ውስጥ ልጃቸውም እንደሙገኝበት ገልፀዋል። እሳቸውንም ፖሊስ እያፈላለገ መሆኑን አመልክተዋል።
እስሩ እየተካሄደ ያለው ለምን " የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ " በሚል እንደሆነ አንዳችም ወንጀል እንዳልተፈፀመ ተናግረዋል።
አንድ የወልቂጤ ነዋሪ ደግሞ ወንድማቸው ለወቅታዊ ስበስባ ተብሎ ተጠርቶ መታሰሩን ገልፀዋል።
የደቡብ ክልል ፖሊስ የዞን ስራ ኃላፊዎች ጨምሮ ቁጥራቸው ያልተገለፀ ሰዎች መታሰራቸውን የደቡብ ክልል ፖሊስ አረጋግጧል።
የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለማየሁ ማሞ ለሬድዮ ጣቢያው ተከታዩን ቃል ሰጥተዋል ፦
" ... ማንም ሰው ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ በአግባቡ በስርዓት መጠየቅ መነጋገር፣ መወያየት፣ መወሰን መብቱ ነው ነገር ግን ተቀጥረው ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት ነው የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር የዋሉት። ምርመራ እየተጣራባቸው ነው። አሁን በአካባቢው የተለየ የፀጥታ ችግር የለም "
ያንብቡ : https://telegra.ph/VOA-08-24
@tikvahethiopia
" ሰዎች ለምን የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ በሚል እየታሰሩ ናቸው " - ነዋሪዎች
" ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር ውለዋል " - የደቡብ ክልል ፖሊስ
በደቡብ ክልላዊ መንግስት ጉራጌ ዞን ከክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች እየተሰሩ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
እየታሰሩ ከሚገኙት መካከል በዞኑ በኃላፊነት ቦታ ያሉ ጭምር መሆናቸው ተጠቁሟል።
ትላንት ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ አቶ በላቸው ገብረማርያን የተባሉ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ የዞኑ ነዋሪ ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ 13 ሰዎች እንደታሰሩ ከነዚህ ውስጥ ልጃቸውም እንደሙገኝበት ገልፀዋል። እሳቸውንም ፖሊስ እያፈላለገ መሆኑን አመልክተዋል።
እስሩ እየተካሄደ ያለው ለምን " የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ " በሚል እንደሆነ አንዳችም ወንጀል እንዳልተፈፀመ ተናግረዋል።
አንድ የወልቂጤ ነዋሪ ደግሞ ወንድማቸው ለወቅታዊ ስበስባ ተብሎ ተጠርቶ መታሰሩን ገልፀዋል።
የደቡብ ክልል ፖሊስ የዞን ስራ ኃላፊዎች ጨምሮ ቁጥራቸው ያልተገለፀ ሰዎች መታሰራቸውን የደቡብ ክልል ፖሊስ አረጋግጧል።
የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለማየሁ ማሞ ለሬድዮ ጣቢያው ተከታዩን ቃል ሰጥተዋል ፦
" ... ማንም ሰው ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ በአግባቡ በስርዓት መጠየቅ መነጋገር፣ መወያየት፣ መወሰን መብቱ ነው ነገር ግን ተቀጥረው ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት ነው የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር የዋሉት። ምርመራ እየተጣራባቸው ነው። አሁን በአካባቢው የተለየ የፀጥታ ችግር የለም "
ያንብቡ : https://telegra.ph/VOA-08-24
@tikvahethiopia
👍456👎127😢42😱18🙏14🥰1
#SNNPRS #SouthWestEthiopia
የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑ ዛሬ ተገልጿል።
በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦
👉 ለወንዶች 41፣
👉 ለሴቶች 40 እና
👉 ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።
በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።
ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።
በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።
በዚህም መሰረት ፦
👉 ለወንዶች 39፣
👉 ለሴቶች 38 እና
👉 ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።
የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።
#ENA
@tikvahethiopia
የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑ ዛሬ ተገልጿል።
በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦
👉 ለወንዶች 41፣
👉 ለሴቶች 40 እና
👉 ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።
በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።
ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።
በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።
በዚህም መሰረት ፦
👉 ለወንዶች 39፣
👉 ለሴቶች 38 እና
👉 ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።
የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።
#ENA
@tikvahethiopia
👍694👎46🙏23❤21😱20🥰6😢6👏2
ሰሞነኛው ዝናብ ...
በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከሰሞኑን እየጣለ ያለው ዝናብ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።
#SNNPRS
በደቡብ ክልል ፥ ጎፋ ዞን ዑባ-ደብረፀሃይ ወረዳ ዛባ ቀበሌ በጣለው ከባድ ዝናብ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ 21 ሰዎች መሞታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በህይወት የተረፉ ዜጎ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲጠለሉ የተደረገ ሲሆን ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማፈላለግ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መገባቱ ተሰምቷል።
ተጎጂ ወገኖችን ለመደገፍም በዞኑ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት ማቋቋሚያ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000511561276 ላይ ድጋፍ እንዲደረግ ተጠይቋል።
#Amhara
በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ 02 አዋተል ቀበሌ ሚያዚያ 27/2015 ዓ.ም ምሽት ለተከታታይ 30 ደቂቃ የጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በእንስሳት፣ በሰብልና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ከ37 ሄክታር መሬት በላይ የደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።
#Gambella
በጋምቤላ ክልል ፤ በዲማ ወረዳና አጎራባች ወረዳዎች ከሚያዝያ 25 /2015 ዓ.ም ጀምሮ እየጣለ ባለው ሃይለኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ በሚሊየን የሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።
የጎርፍ አደጋው እስካሁን ባለው መረጃ በወረዳው ከ70 በላይ መኖሪያ ቤቶች በውሃ ያጥለቀለቀ ሲሆን በሰብል ላይም ጉዳት አድርሷል።
ጎርፉ በዲማ ከተማ ወንዝ ዳር የነበረውን የከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃ መሳቢያ ጀነሬተርና ፖምፕ ግንብ ቤቱን ጨምሮ በሚሊዮን በሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ታውቋል።
በዚህም ችግር ሳቢያ የከተማው ንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት መቆሙ ተነግሯል።
በተመሳሳይ በዲፕ (መርከስ) ቀበሌ የሚገኘው የእኩጉ ስደተኞች መጠለያ ጣብያና የአካባቢው ማህበረሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት የሚሰጡ ሁለት መሳቢያ ጀነሬተሮች በጎርፍ መወሰዱ ታውቋል።
ከዚህ በተጨማሪም የአኮቦ ወንዝ እስከጫፉ ድረስ በመሙላቱ ዲማ ወረዳን ጨምሮ ሁለት አጎራባች ወረዳዎች የሚያገናኝ የአኮቦ ብረት ድልድይ ላይ ጉዳት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች ለማገዝ የክልሉ መንግሥትን ጨምሮ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
መረጃ ምንጮች ፦ የጎፋ ዞን ፣ የለገሂዳ እና የዲማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ናቸው።
@tikvahethiopia
በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከሰሞኑን እየጣለ ያለው ዝናብ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።
#SNNPRS
በደቡብ ክልል ፥ ጎፋ ዞን ዑባ-ደብረፀሃይ ወረዳ ዛባ ቀበሌ በጣለው ከባድ ዝናብ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ 21 ሰዎች መሞታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በህይወት የተረፉ ዜጎ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲጠለሉ የተደረገ ሲሆን ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማፈላለግ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መገባቱ ተሰምቷል።
ተጎጂ ወገኖችን ለመደገፍም በዞኑ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት ማቋቋሚያ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000511561276 ላይ ድጋፍ እንዲደረግ ተጠይቋል።
#Amhara
በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ 02 አዋተል ቀበሌ ሚያዚያ 27/2015 ዓ.ም ምሽት ለተከታታይ 30 ደቂቃ የጣለው በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በእንስሳት፣ በሰብልና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ከ37 ሄክታር መሬት በላይ የደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።
#Gambella
በጋምቤላ ክልል ፤ በዲማ ወረዳና አጎራባች ወረዳዎች ከሚያዝያ 25 /2015 ዓ.ም ጀምሮ እየጣለ ባለው ሃይለኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ በሚሊየን የሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።
የጎርፍ አደጋው እስካሁን ባለው መረጃ በወረዳው ከ70 በላይ መኖሪያ ቤቶች በውሃ ያጥለቀለቀ ሲሆን በሰብል ላይም ጉዳት አድርሷል።
ጎርፉ በዲማ ከተማ ወንዝ ዳር የነበረውን የከተማ ንፁህ መጠጥ ውሃ መሳቢያ ጀነሬተርና ፖምፕ ግንብ ቤቱን ጨምሮ በሚሊዮን በሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ታውቋል።
በዚህም ችግር ሳቢያ የከተማው ንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት መቆሙ ተነግሯል።
በተመሳሳይ በዲፕ (መርከስ) ቀበሌ የሚገኘው የእኩጉ ስደተኞች መጠለያ ጣብያና የአካባቢው ማህበረሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት የሚሰጡ ሁለት መሳቢያ ጀነሬተሮች በጎርፍ መወሰዱ ታውቋል።
ከዚህ በተጨማሪም የአኮቦ ወንዝ እስከጫፉ ድረስ በመሙላቱ ዲማ ወረዳን ጨምሮ ሁለት አጎራባች ወረዳዎች የሚያገናኝ የአኮቦ ብረት ድልድይ ላይ ጉዳት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖች ለማገዝ የክልሉ መንግሥትን ጨምሮ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
መረጃ ምንጮች ፦ የጎፋ ዞን ፣ የለገሂዳ እና የዲማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ናቸው።
@tikvahethiopia
👍377😢163❤69😱12👎10🕊5🥰3