TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UNSC

አሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ፣ አይርላንድ፣ ኖርዌይ እና አልባኒያ በኢትዮጵያ ጉዳይ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባ እንዲያካሂድ ጠይቀው የነበር ቢሆንም በም/ቤቱ ባለው አመግባባት ሳቢያ መካሄዱ እንደሚዘገይ ተሰምቷል።

ከዲፕሎማቶች ሰማሁኝ ብላ የአልጀዚራዋ ጋዜጠኛ አማንዳ ፕራይስ እንደገለፀችው ፤ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ለመነጋገር ተጠይቆ የነበረው ለዛሬ ሀሙስ ቢሆንም እስከሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ሊዘገይ ይችላል።

ይህ የሆነውም ስብሰባው በዝግ ወይስ ክፍት ሆኖ በግልፅ ይካሄድ በሚለው ላይ በምክር ቤቱ አባላት ውስጥ ባለው አለመግባባት መሆኑ ተጠቁሟል።

በሌላ በኩል ፤ ተመድ ያቋቋመው የአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ኤክስፐርቶች ኮሚሽን በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል ዳግም ያገረሸው ግጭት እንደሚያሳስበው ባወጣው  መግለጫ ገልጿል።

ኮሚሽኑ የኤርትራ ወታደሮችም በጦርነት ውስጥ እየተሳተፉ ይገኛሉ ያለ ሲሆን ይህም ግጭቱ ወደ ሌሎች ሀገራት እንዳይዛመት ስጋት አለኝ ብሏል።

ኮሚሽኑ ሁሉም ወገኖች በአስቸኳይ ግጭት እንዲያቆሙና ወደ ውይይት ሂደቱ እንዲመለሱ በድጋሚ ጥሪዬን አቅርባለሁ ብሏል።

በቀጠናው ሰላምና ፀጥታ ላይ ካለው ስጋት አንፃርም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ የኢትዮጵያን ሁኔታ መመልከቱን ኮሚሽኑ እንደሚቀበለው በመግለጫው አሳውቋል።

ኮሚሽኑ ፤ ምክር ቤቱ የሲቪል ዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና ቀጣናውን የበለጠ ሊያናጉ የሚችሉ ግጭቶችን ለመከላከል በወጣው ቻርተር መሰረት እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል።

የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባትም ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ቀንድ ሁኔታዎችን አጀንዳው አድርጎ እንዲቀጥልም ኮሚሽኑ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
👍294👎113😢1110😱10🥰7🙏4
#UNSC

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት " የአፍሪካ ሰላምና ጸጥታ " በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ትላንት መክሮ ነበር።

ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት A3 (ኬንያ፣ ጋቦንና ጋና) የነበሩ ሲሆን በዝግ ነው የተካሄደው።

የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ከስብሰባው በኃላ አንድ የጋራ መግለጫ ለማውጣት ሳይስማማ ቀርቷል።

ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ አንድ የጋራ መግለጫ ማውጣት ሳይችል የቀረው ቻይና እና ሩስያ ባለመደገፋቸው ምክንያት መሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
👍1.57K👎10761🕊42🙏21😱19😢4