#SomaliRegion
የሶማሊ ክልል ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፤ የሶማሊኛ ቋንቋን ያሳድጋል ፤ ይጠብቃል የተባለውን በሶማሊኛ የተዘጋጁ የወራት ስያሜዎች ስራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል።
የክልሉና ሌሎች ባለሞያዎች በሶማለኛ የወር ስያሜዎች ላይ ያካሄዷቸው ጥናቶች ላይ ትላንት ውይይት ተካሂዶ ነበር።
በውይይቱ ላይ ባለሞያዎቹ በሶማሊኛ ቋንቋ በቀን ፤ በወርና በአመት ላይ የተከናወነውን ጥናት የሚያሳይ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል።
የክልሉ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፤ በሶማሊኛ ቋንቋ የተዘጋጀው የወራት ስያሜዎችን እንዳደነቀና ይህም የሶማለኛ ቋንቋን ለማሳደግና ለመጠበቅ ጠቀሜታ እንዳለው መግለፁ ተመላክቷል።
የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ከታች የተዘረዘሩትን የሶማሊኛ ቋንቋ የወር ስያሜዎች ከትላንት ጀምሮ የክልሉ መንግስት ስራ ላይ እንዲውል ውሳኔ አሳልፏል።
1. ኮድሂን / መስከረም / September
2. ዲሪር / ጥቀምት / October
3. ጉድባ / ህዳር / November
4. ሆሬይ / ታህሳስ / December
5. ደርበለይ / ጥር / January
6. አሪር / የካቲት / February
7. ኡር / መጋቢት / March
8. ዱጋቶ / ሚያዚያ / April
9. ሚአድ / ግንቦት / May
10. አጋሊ / ሰኔ / June
11. አፍጋል / ሀምሌ / July
12. ነፍ / ነሀሴ / August
#SRTVAmharic
@tikvahethiopia
የሶማሊ ክልል ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፤ የሶማሊኛ ቋንቋን ያሳድጋል ፤ ይጠብቃል የተባለውን በሶማሊኛ የተዘጋጁ የወራት ስያሜዎች ስራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል።
የክልሉና ሌሎች ባለሞያዎች በሶማለኛ የወር ስያሜዎች ላይ ያካሄዷቸው ጥናቶች ላይ ትላንት ውይይት ተካሂዶ ነበር።
በውይይቱ ላይ ባለሞያዎቹ በሶማሊኛ ቋንቋ በቀን ፤ በወርና በአመት ላይ የተከናወነውን ጥናት የሚያሳይ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል።
የክልሉ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፤ በሶማሊኛ ቋንቋ የተዘጋጀው የወራት ስያሜዎችን እንዳደነቀና ይህም የሶማለኛ ቋንቋን ለማሳደግና ለመጠበቅ ጠቀሜታ እንዳለው መግለፁ ተመላክቷል።
የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ከታች የተዘረዘሩትን የሶማሊኛ ቋንቋ የወር ስያሜዎች ከትላንት ጀምሮ የክልሉ መንግስት ስራ ላይ እንዲውል ውሳኔ አሳልፏል።
1. ኮድሂን / መስከረም / September
2. ዲሪር / ጥቀምት / October
3. ጉድባ / ህዳር / November
4. ሆሬይ / ታህሳስ / December
5. ደርበለይ / ጥር / January
6. አሪር / የካቲት / February
7. ኡር / መጋቢት / March
8. ዱጋቶ / ሚያዚያ / April
9. ሚአድ / ግንቦት / May
10. አጋሊ / ሰኔ / June
11. አፍጋል / ሀምሌ / July
12. ነፍ / ነሀሴ / August
#SRTVAmharic
@tikvahethiopia
👍2.13K👎351🤔109❤108🕊40😢32🥰30🙏27😱18
#ONLF #SOMALIREGION
ከሰሞኑን ተቃዋሚው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ' የሶማሌ ክልል የዜጎች መብት የሚጣስበት እየሆነ ነው " ሲል ከሷል።
ፓርቲው ክልሉ ሶማሌዎች ማንነታቸውን እንዲክዱ የሚገደዱበት እየሆነ ነው ብሏል።
የክልሉን ስያሜና ሰንደቀላማ የመቀየር እቅድ እንዳለ ከአሉባልታ ከፍ ያለ መረጃ አለን ሲሉም፣ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አብዲራህማን መሀዲ ተናግረዋል።
ባለፉት 6 አመታት በክልሉ የጎሳ ግጭቶች ጨምረዋል ሲሉም ወቀሳ አቅርበዋል።
የክልሉ ርዕሰመስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ በበኩላቸው፣ የክልሉ የሀገር ሽማግሌዎች " እኛ ሶማሌዎች እንጂ ሶማሊያውያን አይደለንም " ማለታቸው ማንነትን እንደመካድ ሊወሰድባቸው አይገባም ብለዋል።
በቀድሞው አስተዳደር ህግን ባልተከተለ መንገድ ተቀይሮ የነበረውን ስያሜና ሰንደቅ አላማ በመተው በህገመንግስቱ የተቀመጠውን ስያሜ መጠቀም የጀመረው የእርሳቸው አስተዳደር መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ሙስጠፋ የኦብነግ ሊቀመንበር የሚመሩት ቡድን ይህንን መግለጫ ያወጣው በክልሉ ችግር ስላለ ሳይሆን " ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ እየተስተዋለ ያለውን ጂኦፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ ጥቅም በመፈለግ ነው " ሲሉ ተችተዋል። #ቪኦኤ
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን ተቃዋሚው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ' የሶማሌ ክልል የዜጎች መብት የሚጣስበት እየሆነ ነው " ሲል ከሷል።
ፓርቲው ክልሉ ሶማሌዎች ማንነታቸውን እንዲክዱ የሚገደዱበት እየሆነ ነው ብሏል።
የክልሉን ስያሜና ሰንደቀላማ የመቀየር እቅድ እንዳለ ከአሉባልታ ከፍ ያለ መረጃ አለን ሲሉም፣ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አብዲራህማን መሀዲ ተናግረዋል።
ባለፉት 6 አመታት በክልሉ የጎሳ ግጭቶች ጨምረዋል ሲሉም ወቀሳ አቅርበዋል።
የክልሉ ርዕሰመስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ በበኩላቸው፣ የክልሉ የሀገር ሽማግሌዎች " እኛ ሶማሌዎች እንጂ ሶማሊያውያን አይደለንም " ማለታቸው ማንነትን እንደመካድ ሊወሰድባቸው አይገባም ብለዋል።
በቀድሞው አስተዳደር ህግን ባልተከተለ መንገድ ተቀይሮ የነበረውን ስያሜና ሰንደቅ አላማ በመተው በህገመንግስቱ የተቀመጠውን ስያሜ መጠቀም የጀመረው የእርሳቸው አስተዳደር መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ሙስጠፋ የኦብነግ ሊቀመንበር የሚመሩት ቡድን ይህንን መግለጫ ያወጣው በክልሉ ችግር ስላለ ሳይሆን " ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ እየተስተዋለ ያለውን ጂኦፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ ጥቅም በመፈለግ ነው " ሲሉ ተችተዋል። #ቪኦኤ
@tikvahethiopia
🙏189❤83🕊22😡19🤔18🥰10😱6😭5😢3