TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ArbaMinch

በኢትዮጵያ ግዙፍ ነው የተባለለት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በዛሬው ዕለት ተመረቀ።

ሆስፒታሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ነው የተመረቀው።

ስለ ሆስፒታሉ ፦

- የሆስፒታሉ ግንባታ የተጀመረው በመጋቢት 29 /2007 ዓ/ም ነው።

- ለግንባታ 1.4 ቢሊዮን ብር ወጪ ወጥቶበታል።

- 25 ሺህ ካሬ ላይ ነው ያረፈው።

- አሁን ላይ እጅግ ዘመናዊ የተባሉ የሕክምና መስጫና የምርምራ ቴክኖሎጂዎች አሉት።

- 600 ደረጃቸውን የጠበቁ አልጋዎች አሉት።

- የሄሊኮፕተር አምቡላንስ አገልግሎት የሚሰጥበት ቦታ አለው።

- የውስጥ ደዌ ፣ የቀዶ ጥገና ፣ የሕጻናትና እናቶች ፣ የማህጸን ጽንስ ፣ ከአንገት በላይ፣ የአጥንትና የስነ አእምሮ ... ሌሎችም ህክምናዎች ይሰጡበታል።

- ኦክሲጅን የሚመረትበት ክፍል / ኦክሲጅኑም በየክፍሉ የሚያዳርስ መስመር ፣ የዲጅታል ኤክስሬይ ማሽን ፣ ሲቲ ስካን ፣ ኤም አር አይ ፣ ዘመናዊ አልትራ ሳውንድ ማሽኖች አሉት።

- በሙሉ አቅሙ ስራ ሲጀምር 100 ስፔሻሊስት ሐኪሞች እና ከ2 ሺህ በላይ ሰራተኞች አገልግሎት ይሰጡበታል።

- ከ7 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የአካባቢውና የአጎራባች ክልሎች፣ ዞኖች ነዋሪዎች በአጠቃላይና በስፔሻሊቲ ደረጃ አገልግሎት ይሰጣል።

#SouthEthiopiaRegion
#ArbaMinch

Photo Credit - PM Dr. Abiy Ahmed

@tikvahethiopia
👏1.92K358🙏66🕊46😡39🥰28😢26😭22🤔21😱16
#Arbaminch

በአርባ ምንጭ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚሰሩ ህጻዎች ከፍታቸው G+6 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ስታንዳርድ ተቀመጠ።

የከተማ ህንፃ ቀለማት ምርጫም ነጭና ቢጫ ውህድ ፤ አንድ ህንፃ መቀባት ያለበትም ሶስት አይነት ቀለም ብቻ ነው ተብሏል።

" በኮሪደር የሚለሙ ቋሚ አጥር ግንባታ 1.50 ሜትር ፤ በሚካሄዱ ግንባታዎች ጊዜያዊ አጥሮች ከሁለት ሜትር በላይ ከፍታ ያላቸው ሆነው አረንጓዴ ቀለም በኤጋ ቆርቆሮ ማጠር " እንደሚገባ ተገልጿል።

ዝቅተኛ ህንፃዎች ከመንገድ መራቅ ያለባቸው ርቀት (set back) አደባባዮች ዙሪያ 6 ሜትር፣ ለሌች መንገዶችን ተከትሎ 4 ሜትር፣ ከግለሰቦች ወሰን በኩል መሰኮት ከሌለው 2 ሜትር፣ መስኮት ካለው 3 ሜትር ርቀት መኖር አለበት ተብሏክ።

ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በቀንና በማታ ዕይታን የማይረብሽ ውብና ሳቢ መንገድ ዳር መብራት ቀለም የመብራት ቀለም ከ3000K Warm LED በከተማው በሁሉም ዋና መስመሮች በከተማ ውስጥ ያሉ ንግድና ግለሰብ ቤቶች፣ ድርጅቶችና መንግስታዊ እና ሌሎች ተቋማት የማውጣት ግዴታ እንዳለባቸው ስታንዳርድ ተቀምጧል።

አዲስ አበባ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ወደ ክልሎችም የሄደ ሲሆን የኮሪደር ስራ እየተሰራባቸው ካሉ ከተሞች አንዷ አርባ ምንጭ ናት።

@tikvahethiopia
👏545😡189117😢75🤔41😭23🙏21😱18🥰15🕊11
#ArbaMinch : ላለፉት በርካታ ዓመታት አርባ ምንጭ ላይ ሲገነባ የቆየው የጋሞ አደባባይ ተመርቋል።

" አደባባዩ በዞኑ የሚገኙ ህዝቦችን ባህል እና ትዉፊት በሚወክል መልኩ ነው የተሰራው " ሲል የዞኑ አስተዳደር ገልጿል።

ለዚህ አደባባይ ከ122,000,000 ብር (መቶ ሃያ ሁለት ሚሊዮን ብር) በላይ ወጪ እንደተደረገበት ነው የተነገረው።

@tikvahethiopia
😱1.61K😡841387😭257👏153🤔152🕊79🙏50🥰42😢37
#ArbaMinch

🔴 የእሳት አደጋ መድረሱን ተከትሎ የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ እናት ህይወት አለፈ።

በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ረፋድ 4 ሠዓት አከባቢ በተለምዶ ' ቡቡ ሜዳ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሚገኘዉ አዲሱ ገበያ የእሳት አደጋ ተከስቶ በንብረት ላይ ዉድመት ማድረሱን የከተማው አስተዳደር ፖሊስ አስታውቋል።

በእሳት አደጋዉም የሰዉ ሕይወት መጥፋቱን የሚገልፁ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን ማብራሪያ ጠይቋል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ፤ በአከባቢው በሚገኝ አንድ የኤሌክትሮንክስ ሱቅ ዉስጥ በኤሌክትሪክ ኮንታክት ምክንያት በተነሳ የእሳት አደጋ 12 ሱቆች መዉደማቸዉን ገልጸዋል።

በአደጋው ወቅት በገበያው ዉስጥ በተለምዶ መንገድ በጩኸት ይድረሱልን ጥሪ ሲያደርጉ ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዲት እናት ባለባቸው የጤና እክል ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እኚህ እናት የልብ ሕመም እንደነበራቸው የገለጹት ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ፤ በጩኸት የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ ሳለ በመድከማቸው ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማርተፍ አልተቻለም ነው ያሉት።

ሆኖም በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሕይወቷ ያለፈዉ በእሳት አደጋዉ በደረሰ ጉዳት ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነዉ ብለዋል።

በገበያዉ ዉስጥ ያለዉ የሱቆች አሰራር እና አጠቃቀም ለእሳት አደጋ አጋላጭ ነዉ ያሉት አዛዡ ፤ ሕይወቷ ያለፈዉ ግለሰብ በገበያው ዉስጥ ሱቅ እንደነበራቸውና ሱቃቸዉም እሳት አደጋዉ እንዳልደረሰበት ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእሳት አደጋዉ በተገለፀው አኳሃን መፈጠሩን በገበያው ውስጥ ካሉ ነጋዴዎች የሰማ ሲሆን ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብም በቀጥታ በእሳት አደጋው በደረሰ ጉዳት አለመሆኑን ነጋዴዎች ተናግረዋል።

" ሞች ወ/ሮ አበባየሁ መንገሻ እንደ እናት ያሳደጉኝ እናቴ ናቸዉ፤ የሞቱት በእሳት አደጋዉ አይደለም " ያሉት አቶ አማኑኤል ሰይፉ የተባሉ ነጋዴ አስቀድመው የልብ ሕመምና የሕክምና ክትትል እንደነበራቸው አስረድተዋል።

አክለው በእሳት አደጋዉ ወቅት መደንገጣቸዉና ከሌሎችም ሴቶች ጋር ሆነዉ ለይድረሱልን ብዙ መጮኻቸዉን ተከትሎ መዳከማቸዉንና ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማለፉን ነው የገለጹት።

#TikvahEthiopiaFamilyArbaMinch

@tikvahethiopia
😭1.59K😢199149🕊64😡31🙏21😱19🥰17👏16🤔15