#HPR
በዛሬው ዕለት የሕዝብ ተወካዮች ምክርት ባካሄደው ሶስተኛ ልዩ ስብሰባ የቀረበለትን የ120 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል።
የተጨማሪ በጀት ውሳኔው በዘጠኝ ተቃውሞ በሰባት ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።
በምክር ቤቱ ከጸደቀው በጀት ውስጥ 90 ቢሊየኑ ለአገር መከላከያ ሰራዊት ስንቅና ትጥቅ እንደሚውል ተነግሯል።
ለዕለት ደራሽ ዕርዳታ 8 ቢሊየን ብር፣ ለመጠባበቂያ በጀት 5 ቢሊዮን ብር፣ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ 7 ቢሊዮን ብር እና ለታክስ ገቢ ጉድለት ማካካሻ 9 ቢሊዮን ብር ፀድቋል።
ተጨማሪ በጀቱ የተቋረጡ እና በጅምር ላይ ያሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ለማስቀጠል እንዲሁም በጦርነቱና በኮቪድ 19 ምክንያት በቂ ያለተሰበሰበውን ታክስ ጉድልት ለመሙላት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ቀደም ሲል ለ2014 በጀት አመት 561 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የፌደራል መንግስቱ በጀት ሆኖ በምክር ቤቱ መፅደቁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት የሕዝብ ተወካዮች ምክርት ባካሄደው ሶስተኛ ልዩ ስብሰባ የቀረበለትን የ120 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል።
የተጨማሪ በጀት ውሳኔው በዘጠኝ ተቃውሞ በሰባት ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።
በምክር ቤቱ ከጸደቀው በጀት ውስጥ 90 ቢሊየኑ ለአገር መከላከያ ሰራዊት ስንቅና ትጥቅ እንደሚውል ተነግሯል።
ለዕለት ደራሽ ዕርዳታ 8 ቢሊየን ብር፣ ለመጠባበቂያ በጀት 5 ቢሊዮን ብር፣ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ 7 ቢሊዮን ብር እና ለታክስ ገቢ ጉድለት ማካካሻ 9 ቢሊዮን ብር ፀድቋል።
ተጨማሪ በጀቱ የተቋረጡ እና በጅምር ላይ ያሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ለማስቀጠል እንዲሁም በጦርነቱና በኮቪድ 19 ምክንያት በቂ ያለተሰበሰበውን ታክስ ጉድልት ለመሙላት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ቀደም ሲል ለ2014 በጀት አመት 561 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የፌደራል መንግስቱ በጀት ሆኖ በምክር ቤቱ መፅደቁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
👍351👎122❤12🔥9😁5😢5😱1