TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DireDawa

#ማሻሻያ

በድሬዳዋ አስተዳደር እሁድ ጠዋት ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዝግ እንዲሆን የተወሰነው ውሳኔ ላይ ማሻሻዮች ተደርጎበታል።

በድሬዳዋ አስተዳደር በሳምንቱ መጨረሻ እሁድ ላይ ከጠዋት 12 ሰአት እስከ 4 ሰአት ድረስ በከተማዋ ላይ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዝግ ከመደረጉ ጋር ተያይዞ ከዚህ ቀደም በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆይተዋል ።

በዚሁም ጉዳይ ዙሪያ ዛሬ ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ተካሂዷል ።

በተለይም እድሜያቸው የገፍ እናት አባቶች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እሁድ ወደ ቤተ-እምነቶች ለመሄድ የትራንስፖርት አገልግሎት ካለመኖሩ ጋር ተያይዞ በእጅጉ እየተቸገሩ ከመሆናቸው ባለፈ የጤና እክል ያለባቸው አካላትም ረጅም እርቀት በእግር ለመሄድ መቸገራቸውንም የሀይማኖት አባቶቹ በውይይቱ ላይ አንስተዋል።

ስለሆነም ማሻሻያ እንዲደረግ ጠይቀዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር እሁድ ጠዋት በከተማዋ ላይ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዝግ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከነዋሪው ህብረተሰብ እንዲሁም ከሀይማኖት አባቶች የተነሱትን ጥያቄዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት እሁድ ጠዋት ሙሉ ከተማው ለትራንስፖርት ክፍት እንዲሆን መወሰኑን አሳውቀዋል።

ነገር ግን ከኮኔል ድልድይ አንስቶ ከዚራ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ለትራንስፖርት ዝግ እንደሚሆንም ከንቲባው ተናግረዋል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

ምንጭ፦ የድሬዳዋ ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
👍1
TIKVAH-ETHIOPIA
የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል ተብሏል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከሰኔ 23 / 2015 እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ባለበት እንደሚቀጥል አስታውቋል። በዚሁ መሠረት ፦ 1. ቤንዚን 👉 በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም 2. ነጭ ናፍጣ 👉 በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም በሊትር…
የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

የሁሉም ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሀምሌ ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

በዚሁ መሠረት ፦

1. ቤንዚን 👉 በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም

2. ነጭ ናፍጣ 👉 በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም በሊትር

3. ኬሮሲን 👉 በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም

4. የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 በሊትር 65 ብር ከ35 ሳንቲም

5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 በሊትር 57 ብር ከ97 ሳንቲም

6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 በሊትር 56 ብር ከ63 ሳንቲም ይሸጣል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በመጪዎቹ ጊዜያት የአለም የነዳጅ ገበያን መነሻ በማድረግ አስፈላጊው #ማሻሻያ የሚደረግ መሆኑን አመልክቷል።

@tikvahethiopia
👍315👎3528🙏6👏3🕊3😱2😭1