TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 7 ነው " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት የፊታችን ሰኞ መስከረም 7 /01/2016 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ተቋማት እንደሚጀምር አስታወቀ።
ቢሮው ይህን ያሳወቀው የትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ/ም የትምህርት ካላንደርን ለህዝብ ካሰራጨ በኃላ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው አጭር መልዕክት ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ፤ " የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 14 /1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #የተሳሳተ ነው " ብሏል።
ቢሮው በየትኞቹ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተሳሳተ መረጃ እንደተሰራጨ በግልፅ አላሰፈረም።
የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ ባደረገው የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት #ሀገር_አቀፍ የትምህርት ካላንደር መሰረት ከመስረም 7 እስከ 11/2016 ዓ/ም ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል።
መስከረም 14 ደግሞ የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ካላንደሩ ላይ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ #የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ ብሏል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው መሰረት የ2016 ዓ/ም ትምህርት ሰኞ መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ/ም በሁሉም ተቋም እንደሚጀምር #አስረግጦ ተናግሯል ፤ መላው የትምህርት ማህበረሰብ ይህን እንዲያውቀው ብሏል።
ከቀናት በፊት የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ/ም የትምህርት መስከረም 7/2016 ዓ/ም እንደሚጀምር ማሳወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት የፊታችን ሰኞ መስከረም 7 /01/2016 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ተቋማት እንደሚጀምር አስታወቀ።
ቢሮው ይህን ያሳወቀው የትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ/ም የትምህርት ካላንደርን ለህዝብ ካሰራጨ በኃላ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው አጭር መልዕክት ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ፤ " የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 14 /1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #የተሳሳተ ነው " ብሏል።
ቢሮው በየትኞቹ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተሳሳተ መረጃ እንደተሰራጨ በግልፅ አላሰፈረም።
የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ ባደረገው የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት #ሀገር_አቀፍ የትምህርት ካላንደር መሰረት ከመስረም 7 እስከ 11/2016 ዓ/ም ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል።
መስከረም 14 ደግሞ የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ካላንደሩ ላይ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ #የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ ብሏል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው መሰረት የ2016 ዓ/ም ትምህርት ሰኞ መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ/ም በሁሉም ተቋም እንደሚጀምር #አስረግጦ ተናግሯል ፤ መላው የትምህርት ማህበረሰብ ይህን እንዲያውቀው ብሏል።
ከቀናት በፊት የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ/ም የትምህርት መስከረም 7/2016 ዓ/ም እንደሚጀምር ማሳወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
@tikvahethiopia
👍1.57K👎690❤226😢155🕊56😱48🙏37🥰18
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዜዳንቶች በቅርቡ ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት እንዳደረጉ ቪኦኤ ዘግቧል። የክልሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ፀሀፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ የዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዜዳንቶች ባደረጉት ውይይት ወቅታዊው የክልሉ የፀጥታ ችግር በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ…
#Amhara
በአማራ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን፤ የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎችን አቋም በተመለከተ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረው መረጃ " #የተሳሳተ ነው " አሉ።
ከሰሞኑን በአማራ ክልል ስላሉ ዩኒቨርሲቲዎች ምንድነው የተባለው ?
ከቀናት በፊት ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የፎረሙን ዋና ጸሐፊ የሆኑትን ዶ/ር አስማረ ደጀንን ዋቢ በማድረግ ባወጣውና ቲክቫህ ኢትዮጵያም ባጋራው ዘገባ ፤ በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶች ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት ካደረጉ በኃላ ሁኔታው #በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማስቀጠል የሚያስችል እንዳልሆነ የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።
በተጨማሪ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤
* ተማሪዎች ገብተው ግጭቶች በሚመጡበት ጊዜ ዩኒቨርሲቲዎች ኃላፊነት እንደማይወስዱ፤
* ዩኒቨርሲቲዎች ለ2016 የሚሆን የምግብ አቅርቦት ማዘጋጀት የነበረባቸው ቢሆንም አቅራቢዎቹ ከቦታ ቦታ ፤ ምርት ካለበት ቦታ ሄደው ተዘዋውረው መግዛት ስላልቻሉ የምግብ ግብአቶች በጠቅላላው ተማሪን ሊያስጠራ የሚችል እንዳልሆነ ገልፀዋል።
ፎረሙ ትምህርት ሚኒስቴር " ለ2016 ትምህርት በአሁን ሰዓት ተማሪዎችን ጥሩ እያለ ነው " ብሎ ለፀጥታው ኃላፊነት የሚወስድ አካል ከሌለ ይህን ማድረግ #እንደሚያስቸግር ነው የገለፀው።
ከዚህ ባለፈ የፎረሙ አባልና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ፤ በአካባቢው የቀጠለው አለመረጋጋት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ እንደማያስችል ከተስማሙት የፎረሙ አባላት እንደሆኑ ገልጸዋል።
ያለው ሁኔታ ካልተሻሻለ በስተቀር አሁን ባለው ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ግቢ ውስጥ ተማሪ ማስገባት በእጅጉ ፈታኝ እንደሚሆንና ለልጆችም ደህንነት በጣም አስጊ መሆኑን ፕሬዜዳንቱ ለጣቢያው ተናግረዋል።
ይህ መረጃ ከተሰራጨ ከቀናት በኃላ የፎረሙ ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዛሬ በሰጡት ቃል " ሰሞኑን የተሰራጨው መረጃ በአማራ ክልል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ያልተባለና ስህተት ነው " ብለዋል።
በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ለመቀበል አመች ሁኔታዎችን እየተጠባበቁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን መጥራት መጀመራቸውንም ገልጸው፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ ማስተላለፉን ለአብነት አንስተዋል፡፡
"አብዛኞቹ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን እየጠሩ ነው" ያሉ ሲሆን " ብዙ ተማሪዎችን በአንድ ጊዜ ለመጥራት ግን የግብዓት ችግር ለተቋማቱ እንቅፋት ሆኗል " ብለዋል።
ዶ/ር አስማረ፤ በክልሉ በተፈጠረው የሰላም እጦት ግብዓት አቅራቢዎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ለማቅረብ የተቸገሩ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲዎች የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየሠሩ መሆኑን አሳውቀዋል። በየአካባቢው ያሉ አቅራቢዎች ግብዓት እንዲያቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎችን ተቀበሉ በሚልበት ጊዜ የማይቀበሉበት ምክንያት እንደሌለም ገልጸዋል።
" ክልሉ ያጋጠመው የጸጥታ ችግር እየተሻሻለ ከመጣ ተቋማቱ ተማሪዎቻቸውን ወዲያው ይጠራሉ፤ ተማሪዎችን አይጠሩም የተባለው ስህተት ነው፤ አልተባለምም " ሲሉ ተናግረዋል።
አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ግብዓት ለማግኘት ከመቸገራቸው ውጭ የመማሪያ ክፍሎችን አጽድተዋል፣እድሳት የሚያስፈልጋቸውንም አድሰው ለትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ዝግጁ ሆነዋል ሲሉ ለክልሉ ሚዲያ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን፤ የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎችን አቋም በተመለከተ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረው መረጃ " #የተሳሳተ ነው " አሉ።
ከሰሞኑን በአማራ ክልል ስላሉ ዩኒቨርሲቲዎች ምንድነው የተባለው ?
ከቀናት በፊት ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የፎረሙን ዋና ጸሐፊ የሆኑትን ዶ/ር አስማረ ደጀንን ዋቢ በማድረግ ባወጣውና ቲክቫህ ኢትዮጵያም ባጋራው ዘገባ ፤ በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶች ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት ካደረጉ በኃላ ሁኔታው #በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማስቀጠል የሚያስችል እንዳልሆነ የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።
በተጨማሪ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤
* ተማሪዎች ገብተው ግጭቶች በሚመጡበት ጊዜ ዩኒቨርሲቲዎች ኃላፊነት እንደማይወስዱ፤
* ዩኒቨርሲቲዎች ለ2016 የሚሆን የምግብ አቅርቦት ማዘጋጀት የነበረባቸው ቢሆንም አቅራቢዎቹ ከቦታ ቦታ ፤ ምርት ካለበት ቦታ ሄደው ተዘዋውረው መግዛት ስላልቻሉ የምግብ ግብአቶች በጠቅላላው ተማሪን ሊያስጠራ የሚችል እንዳልሆነ ገልፀዋል።
ፎረሙ ትምህርት ሚኒስቴር " ለ2016 ትምህርት በአሁን ሰዓት ተማሪዎችን ጥሩ እያለ ነው " ብሎ ለፀጥታው ኃላፊነት የሚወስድ አካል ከሌለ ይህን ማድረግ #እንደሚያስቸግር ነው የገለፀው።
ከዚህ ባለፈ የፎረሙ አባልና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ፤ በአካባቢው የቀጠለው አለመረጋጋት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ እንደማያስችል ከተስማሙት የፎረሙ አባላት እንደሆኑ ገልጸዋል።
ያለው ሁኔታ ካልተሻሻለ በስተቀር አሁን ባለው ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ግቢ ውስጥ ተማሪ ማስገባት በእጅጉ ፈታኝ እንደሚሆንና ለልጆችም ደህንነት በጣም አስጊ መሆኑን ፕሬዜዳንቱ ለጣቢያው ተናግረዋል።
ይህ መረጃ ከተሰራጨ ከቀናት በኃላ የፎረሙ ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዛሬ በሰጡት ቃል " ሰሞኑን የተሰራጨው መረጃ በአማራ ክልል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ያልተባለና ስህተት ነው " ብለዋል።
በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ለመቀበል አመች ሁኔታዎችን እየተጠባበቁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን መጥራት መጀመራቸውንም ገልጸው፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ ማስተላለፉን ለአብነት አንስተዋል፡፡
"አብዛኞቹ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን እየጠሩ ነው" ያሉ ሲሆን " ብዙ ተማሪዎችን በአንድ ጊዜ ለመጥራት ግን የግብዓት ችግር ለተቋማቱ እንቅፋት ሆኗል " ብለዋል።
ዶ/ር አስማረ፤ በክልሉ በተፈጠረው የሰላም እጦት ግብዓት አቅራቢዎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ለማቅረብ የተቸገሩ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲዎች የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየሠሩ መሆኑን አሳውቀዋል። በየአካባቢው ያሉ አቅራቢዎች ግብዓት እንዲያቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎችን ተቀበሉ በሚልበት ጊዜ የማይቀበሉበት ምክንያት እንደሌለም ገልጸዋል።
" ክልሉ ያጋጠመው የጸጥታ ችግር እየተሻሻለ ከመጣ ተቋማቱ ተማሪዎቻቸውን ወዲያው ይጠራሉ፤ ተማሪዎችን አይጠሩም የተባለው ስህተት ነው፤ አልተባለምም " ሲሉ ተናግረዋል።
አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ግብዓት ለማግኘት ከመቸገራቸው ውጭ የመማሪያ ክፍሎችን አጽድተዋል፣እድሳት የሚያስፈልጋቸውንም አድሰው ለትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ዝግጁ ሆነዋል ሲሉ ለክልሉ ሚዲያ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
😭721❤281😡217🙏177🕊99👏52😱41🥰38😢32