TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

" ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " - ዶ/ር ፋና ሀጎስ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት)

ከትላንት ምሽት አንስቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲን የሚመለከቱ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ።

እነዚህ መረጃዎች ፦
- ዩኒቨርሲቲው ወደ መማር ማስተማር ስራው እዲመለስ መወሰኑ፣
- በጦርነቱ አቋርጦ የነበረውን ስራ ከመጪው ሳምንት አንስቶ እንደሚጀምር፣
- በመንግስት በኩል አስፈላጊው #በጀት እንደተለቀቀለት፣
- 24 ሺህ ነባር ተማሪዎችን በቀጣይ 4 ወር ትምህርት እንዲያጠናቅቁ እንደሚያደርግ
- ከመስከረም 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የሚገልፁ ናቸው።

ነገር ግን ይህ የተሳሳተ መረጃ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገልጸዋል።

መቐለ ዩኒቨርሲቲም ቢሆን በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ ምንም አይነት መረጃ አልለጠፈም።

የተሰራጨውን መረጃ በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሀጎስ ለ" ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ ማጣሪያ ድረገፅ በሰጡት ቃል ፥ ዩኒቨርሲቲው ስራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ ቢሆንም በዩኒቨርሲቲው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን የራሱን ጊዜና ሂደት እንደሚወስድ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና " ዩኒቨርሲቲው ሥራውን ይጀምራል ነገር ግን በሚቀጥለው ሳምንት አይደለም ፤ በእርግጥ ይህን ለማድረግ ወራትን ይወስዳል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና እስካሁን መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ እንዳላደረገ ገልፀው " እኛ (ዩኒቨርሲቲው ወይም የትምህርት ሚኒስቴር) ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

Credit : ethiopiacheck.org

@tikvahethiopia
👍1.77K119👎102🤔77🙏66🕊58😱36🥰29😢23
" #ኢትዮጵያን በማስጠራቴ ትልቅ ክብር ይሰማኛል " - የወጣቱ የህዋ ሳይንስ ተመራማሪ ትንሳኤ አለማየሁ

#ኢትዮጵያዊው የሕዋ ሳይንስ ተመራማሪ ወጣት ትንሳኤ አለማየሁ ዓለም አቀፉ የአስትሮኖቲካል ፌደሬሽን የ2023 ወጣት የህዋ መሪዎች ብሎ ከሰየማቸው አምስት ተመራማሪዎች አንዱ ሆኗል።

ፌደሬሽኑ ስያሜውን እውቀታቸውንና ልምዳቸውን ለሌሎች ወጣቶች በማጋራትና ማህበረሰብ በመድረስ እንዲሁም በትምህርት እና ምርምር ለአስትሮኖቲክ መስክ አበርክቶ ላደረጉ ወጣቶች የሚሰጠው ዕውቅና ነው።

ፌደሬሽኑ ሽልማቱን በባኩ አዘርባጃን በመስከረም 2016 ዓ.ም በሚደረገው በ74ኛው የዓለም አቀፉ የአስትሮኖቲካል ኮንግረስ ለወጣት ተመራማሪዎቹ እንደሚሰጥ ተገልጿል።

በዓለም አቀፉ ፌደሬሽን በወጣቶች ዘርፍ የሚሰጠውን ትልቁን ሽልማት በማግኘቱ ከፍተኛ ደስታ እንደሚሰማው ትንሳኤ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግሯል።

ሽልማቱን በማግኘት ኢትዮጵያን በማስጠራቱ ትልቅ ክብር እንደሚሰማውም ገልጿል።

በሜካኒካል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪውን ከ #መቐለ_ዩኒቨርሲቲ ያገኘው ትንሳኤ አለማየሁ ፤ ለህዋ ሳይንስ ባለው ራዕይ እና ለዘርፉ ላደረገው አበርክቶ በርካታ ሽልማቶችን አጊኝቷል። 

ካገኛቸው ሽልማቶች ውስጥ ፦

- እ.ኤ.አ. በ2022 ከዓለም አቀፉ የጠፈር ተመራማሪዎች ፌደሬሽን (አይኤኤፍ) የተበረከተውን ተስፋ የተጣለባቸው ስፔስ መሪዎች ሽልማትን፤

- ከ30 አመት በታች የአፍሪካ ስፔስ ኢንዱስትሪ ሽልማት፤

- በ2021 ከስፔስ ኢን አፍሪካ እና ከSGAC የግሎባል ግራንት ፕሮግራም ሽልማትን፤

- በ2019 ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የወጣት ሕዋ አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች ብዙ ሽልማቶችን እና እውቅናዎችን አግኝቷል።

ወጣቱ ተመራማሪ አሁን ላይ የዓለም ዐቀፉ የህዋ ጄነሬሽን አማካሪ ም/ቤት (SGAC) የአፍሪካ ቀጣናዊ አስተባባሪ በመሆን እያገለገለ ይገኛል።

https://www.iafastro.org/news/the-iaf-is-proud-to-introduce-the-2023-iaf-young-space-leaders.html

More : @tikvahuniversity
👍2.08K266👎28🙏25😱21🥰10😢8🕊7👏1