TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ዳሽን ባንክ ላይ የሲስተም ችግር አጋጥሟል  " የሚለው መረጃ ሐሰተኛ ነው ሲል ባንኩ ገለጸ።

ትላንት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጋጥሞኛል ባለው ሲስተም ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረው አገልግሎቱ ዳግም መስተካከሉ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያው ላይ ዳሽን ባንክም ተመሳሳይ አይነት የሲስተም ችግር ማለትም ሰዎች፦
- ያለገደብ ገንዘብ ከኤቲኤም የማውጣት
- በሞባይል ባንኪንግ ገደብ የሌለው ገንዘብ የማስተላለፍ ችግሮች ገጥሞታል በሚል እየተሳራጨ ይገኛል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይም ሰዎች ወደ ዳሽን ኤቲኤሞች በመሄድ ያለ ገደብ ገንዘብ ማውጣት እንደሚችሉ የሚገልጹ መልዕክቶች እየተዘዋወሩ ነው።

ባንኩ ግን "  ይህ ፍፁም #ሐሰተኛ መረጃ ነው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ገልጿል።

የባንኩ ኤትኤሞች እና የዲጂታል አውታሮች ሁሉ ደህንነታቸው በአስተማማኝ ሁኔታ የተጠበቀ እንደሆነ ገልጾ ደንበኞቹ ምንም አይነት ስጋት ላይ እንዳይወድቁ አስገንዝቧል።

@tikvahethiopia
👏36294🤔57😡26🥰21😱17😭17🙏14😢11🕊8
" በየቤቱ የቁም እንስሳት ማረድ / በየአካባቢው ቅርጫ አድርጎ መከፋፈል አልተከለከለም " - የአዲስ አበባ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ፥ ከትንሳዔ በዓል ጋር በተያያዘ " ህብረተሰቡ በየቤቱ የቁም እንስሳት እርድ በማካሄድ ወይም በየአካባቢው ቅርጫ በማድረግ የሚከፋፈልበት አሰራር ተከልክሏል " በሚል በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው መረጃ #ሐሰተኛ ነው ሲል አሳወቀ።

ከዚህም ጋር በተያያዘ #ምንም_ዓይነት_ክልከላ ያልተደረገ መሆኑን አረጋግጧል።

ነገር ግን በየአካባቢው #በሕገወጥ_መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት የቁም እንስሳቱ ጤንነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ድርጊቱ በከተማው ነዋሪዎች ጤንነት ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል ብሏል።

የከተማዋ ነዋሪዎችም ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
👏1.67K187🤔88🙏76😡55🕊30😭21😱20😢19🥰14