TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.3K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Australia

የአውስትራሊያ የተወካዮች ም/ቤት ከ16 ዓመት በታች ያሉ አዳጊዎች ማኅበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ የሚያግድ ሕግ አጸደቀ።

ሕጉ በሃገሪቱ የእንደራሴዎች ም/ቤት (ሴኔት) ከጸደቀ በዓለም የመጀመሪያው ይሆናል።

የተወካዮች ም/ቤቱ በ102 ድጋፍ እና 13 ተቃውሞ ድምጽ አጽድቆታል።

በሃገሪቱ የሚገኙ ዋና ፓርቲዎች የደገፉት ሕግ ፦
➡️ ቲክቶክ፣
➡️ ፌስቡክ፣
➡️ ስናፕቻት፣
➡️ ሬዲት፣
➡️ X እና ኢንስታግራም የመሰሉ መድረኮች አዳጊዎች ተጠቃሚ እንዳይሆኑ የማይከላከሉ ከሆነ እስከ 33 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

ሕጉ በዚህ ሳምንት በሴኔቱም የሚጸድቅ ከሆነ፣ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያዎቹ የዕድሜ ገደቡን ተፈጻሚ የሚያደርጉበትን መላ ለመዘየድ አንድ ዓመት ይሰጣቸዋል።

ከአንድ ዓመት ጊዜ በኋላ ግን ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል።

የሃገሪቱ ዋና ዋና ፓርቲዎች ሕጉን በመደገፋቸው፣ በእንደራሴዎች ምክር ቤት ሊጸድቅ እንደሚችል ይጠበቃል ሲል ቪኦኤ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
👏2.21K224🥰24🕊18🙏17😡8😱7😢7🤔5😭4