TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሰማይ ላይ ያየነዉ እንግዳ ነገር ፍርሀት ዉስጥ ጥሎናል " - ነዋሪዎች ዛሬ ምሽት በበአርባ ምንጭ ፣ ወላይታ ሶዶ ፣ ቡርጂ ፣ ሱሮ ባርጉዳ (ምዕራብ ጉጂ ዞን) እና ሌሎችም በርካታ ስፍራዎች በሰማይ ላይ የታየዉ ተምዘግዛጊ ሮኬት መሳይ ተቀጣጣይ ነገር ፍርሃት አንደጫረባቸዉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ " ምሽት 2 ሰዓት ገደማ ሮኬት መሳይ ተቀጣጣይ ብርሃናማ ነገር በሰማይ…
" የማጣራት ሥራውን እስክናጠናቅቅ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ በትህትና እንጠይቃለን " - የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ

የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸው ሪፖርት እንደደረሰው ዛሬ ጥዋት አሳውቋል።

" በደረሰን ተንቀሳቃሽ ምስል ለመመልከት እንደቻልነው የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ " ብሏል።

" ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል " ሲል አክሏል።

" የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ያስችለን ዘንድ ሁኔታውን በቅርበት እያጣራን የምንገኝ ሲሆን ፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል " ብሏል።

" የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ  ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ በትህትና እንጠይቃለን " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

#ESSS

@tikvahethiopia
🤔606169🙏94😭73😡48🕊36😱31😢23🥰15👏4