#ሀላባ
- " ባለቤቴ ከወንድሙና እህቱ ጋር በመሆን ፊቴ እስኪበላሽ ደበደቡኝ " - ተበዳይ
- " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " - የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ሙደሲር ጉታጎ
በሀላባ ከተማ " ባለቤቴ ከእህትና ወንድሙ ጋር በመሆን አደጋ አድርሶብኛል " ያለች ተበዳይ የህግ ድጋፍ ስጡኝ ስትል በማህበራዊ ሚዲያ ጥያቄ አቅርባለች።
ጉዳዩን የተመለከተው የሀዋሳ የቲኪቫህ ቤተሰብ አባል ባደረገዉ ማጣራት ፥ ተጎጅዋ ፊቷ ላይ ጉዳት መደረሱን በተጨማሪ የሷና የመጀመሪያ ልጇ ሰዉነት ትክሻቸዉ አካባቢ ' ጥርስ ንክሻ ' እንደደረሰባቸዉ ለማወቅ ችሏል።
የግል ተበዳዩዋ እናት ለቲክቫ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ ልጃቸዉና የልጅ ልጃቸዉ በደም ተዘፍቀዉ በምሽት ወደቤት እንደመጡና በወቅቱ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገንተው እንደነበር ገልጸዋል።
የግል ተበዳዩዋ ወ/ሮ አበባ ቦረና ፤ " ምንም እንኳን የጋራ አራት ልጆች ቢኖሩንም ካሁን በፊት በመካከላችን በነበረ ግጭት ምክኒያት በፍርድ ቤት ለመለያየት ጫፍ ከደርሰን በኋላ በሽማግሌ ተመልሰን አንድ ላይ መኖር ከጀመርን 3 ወር አልሆነም " ብላለች።
" ምንም እንኳን ቀን ላይ ቀላል ጭቅጭቅ ውስጥ ብንገባም ከቤተሰቡ ጋር ሆኖ እንዲህ ያደርጋል ብዬ ፍጹም አልጠበኩም " ስትል ተናግራለች።
" በተለይ ተሰብስበዉ ሲደበድቡኝ ለመገላገል የገባዉን የመጀመሪያ ልጃችን ላይ ላይ በዚህ ልክ ይጨክናል ብዬ አላሰብኩም ነበር " ብላለች።
ጉዳዩን በተመለከተ የጸጥታ አካላት ምን እየሰሩ ነዉ ? በማለት የጠየቅናቸው የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ አቶ ሙደሲር ጉታጎ ፤ " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " ብለዋል።
ጉዳዩን በሰሙ ቅጽበት የከተማው ፖሊስ በፍጥነት ችግር ፈጣሪዎችን ይዞ እንዲያጣራ ማዘዛቸዉንም ነግረዉናል።
አቶ ሙደሲር ጉዳዩ ተጣርቶ የሚደረስበትን ውጤት እንደሚያጋሩን ቃል ገብተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
- " ባለቤቴ ከወንድሙና እህቱ ጋር በመሆን ፊቴ እስኪበላሽ ደበደቡኝ " - ተበዳይ
- " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " - የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ሙደሲር ጉታጎ
በሀላባ ከተማ " ባለቤቴ ከእህትና ወንድሙ ጋር በመሆን አደጋ አድርሶብኛል " ያለች ተበዳይ የህግ ድጋፍ ስጡኝ ስትል በማህበራዊ ሚዲያ ጥያቄ አቅርባለች።
ጉዳዩን የተመለከተው የሀዋሳ የቲኪቫህ ቤተሰብ አባል ባደረገዉ ማጣራት ፥ ተጎጅዋ ፊቷ ላይ ጉዳት መደረሱን በተጨማሪ የሷና የመጀመሪያ ልጇ ሰዉነት ትክሻቸዉ አካባቢ ' ጥርስ ንክሻ ' እንደደረሰባቸዉ ለማወቅ ችሏል።
የግል ተበዳዩዋ እናት ለቲክቫ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ ልጃቸዉና የልጅ ልጃቸዉ በደም ተዘፍቀዉ በምሽት ወደቤት እንደመጡና በወቅቱ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገንተው እንደነበር ገልጸዋል።
የግል ተበዳዩዋ ወ/ሮ አበባ ቦረና ፤ " ምንም እንኳን የጋራ አራት ልጆች ቢኖሩንም ካሁን በፊት በመካከላችን በነበረ ግጭት ምክኒያት በፍርድ ቤት ለመለያየት ጫፍ ከደርሰን በኋላ በሽማግሌ ተመልሰን አንድ ላይ መኖር ከጀመርን 3 ወር አልሆነም " ብላለች።
" ምንም እንኳን ቀን ላይ ቀላል ጭቅጭቅ ውስጥ ብንገባም ከቤተሰቡ ጋር ሆኖ እንዲህ ያደርጋል ብዬ ፍጹም አልጠበኩም " ስትል ተናግራለች።
" በተለይ ተሰብስበዉ ሲደበድቡኝ ለመገላገል የገባዉን የመጀመሪያ ልጃችን ላይ ላይ በዚህ ልክ ይጨክናል ብዬ አላሰብኩም ነበር " ብላለች።
ጉዳዩን በተመለከተ የጸጥታ አካላት ምን እየሰሩ ነዉ ? በማለት የጠየቅናቸው የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ አቶ ሙደሲር ጉታጎ ፤ " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " ብለዋል።
ጉዳዩን በሰሙ ቅጽበት የከተማው ፖሊስ በፍጥነት ችግር ፈጣሪዎችን ይዞ እንዲያጣራ ማዘዛቸዉንም ነግረዉናል።
አቶ ሙደሲር ጉዳዩ ተጣርቶ የሚደረስበትን ውጤት እንደሚያጋሩን ቃል ገብተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
😡1.34K😭253❤147😢82🤔44🙏40🕊34😱30👏25🥰9