TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.3K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#FightCOVID19

- የአዲስ አበባ ከተማ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ከሜድሮክ ኢትዮዽያ ኢትዮ አግሪሴፍ የተረከባቸውን 45 የደለቡ በሬዎች 'ማዕድ ማጋራት' በሚል ለአርባ ሰፈሮች በቄራዎች ድርጅት ጤናማነቱን ያረጋገጥ እርድ ተከናውኖ እንድሰራጭ በቄራዎች ድርጅት ግቢ ርክክብ ተደርጎል። የስጋ ስርጭቱን የአ.አ ቄራዎች ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ሰይድ እንድሪስ እና ከአርባ ሰፈር በጎ ፈቃደኞች ወጣቶች ጋር በመተባበር ለመስራት ቃል ገብተዋል።

- አትሌት መሰረት ደፋር መገናኛ አካባቢ እያስገነባች ያለውን ባለ 12 ወለል ሕንጻ ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል ለለይቶ ማቆያነት እንዲያገለግል አስረክባለች።

- ራይድ #RIDE የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ጥረት በተለያዩ የህክምና ተቋማት እያገለገሉ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች እንዲሆን 50,000 የአፍ መሸፈኛ ማስኮችን ለኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ማህበር አስረክቧል።

- ጋስት ሶላር መካኒክስ ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የያዛቸው ታካሚዎች አተነፋፈሳቸውን የሚያግዝ ቱቦ ወደ አየር ቧንቧቸው ሲገባ እንደ መከላከያ የሚያግዝ መሳሪያ ለጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እገዛ አድርጓል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot