TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ETHIOPIA

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር መግለጫቸው ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገው በሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በሚመለከት ነው።

በመግለጫቸው ምን አሉ ?

- 391 የሚደርሱ ሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ተዘግቷል ፤ የግለሠቦቹን ስም ዝርዝር ለፍትሕ ሚኒስቴር በመላክ ክስ የመመስረት ሂደት ይጀመራል።

- በህገ ወጥ መልኩ #በጥቁር_ገበያ ላይ በተሠማሩ አካላት ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይወሰዳል።

- በባንክ ቤቶች ውስጥ ያሉ የባንክ #ኃላፊዎችና #ሰራተኞችም በህገወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አሉ በነዚህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃና ሕጋዊ እርምጃ ይወሰዳል።

- ሕገወጥ ድርጊት ለሚጠቁሙ ዜጎች የወሮታ አከፋፈል ስርዓት ተዘጋጅቷል።

ይህ ማለት ፦

• ከተፈቀደው በላይ በቤት ውስጥ የብር ክምችት የሚያደርጉ፣

• የሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን የሚሠሩና የሚያሠራጩ አካላት፣

• በህገወጥ መልኩ የሐዋላ አገልግሎት የሚሠጡ ወይም በጥቁር ገበያ ላይ የተሰማሩ አካላትን ለሚጠቁሙ ዜጎች #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸውን በጠበቀ መልኩ #የሚሸልምና #ወረታውን የሚከፈል ይሆናል።

- የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር የፈቀደውን የፍራኮ ቫሉታ ፍቃድ እንደ እድል በመጠቀም በህገወጥ መንገድ ዶላር በመጠቀም ሸቀጦችን የማስገባት ተግባር የተስተዋለ በመሆኑ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች የባን ማስረጃ ለብሔራዊ ባንክ እንዲያቀርቡ ይደረጋል።

Credit : EPA

@tikvahethiopia
👍939👎111😢18🕊1716🙏13😱8
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር መግለጫቸው ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገው በሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በሚመለከት ነው። በመግለጫቸው ምን አሉ ? - 391 የሚደርሱ ሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ተዘግቷል ፤ የግለሠቦቹን ስም ዝርዝር ለፍትሕ ሚኒስቴር በመላክ ክስ የመመስረት ሂደት ይጀመራል። …
የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ፦

- ኢትዮጵያዊያን በግለሰብ ደረጃ ከ100 ሺህ ብር በላይ ለድርጅቶች ደግሞ ከ200 ሺህ ብር በላይ ቤት ውስጥ ማስቀመጥ የተከለከለ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸወል።

- ገንዘብ በባንክ መቀመጥ አለበት ፤ የግብይት ስርዓትም በባንክ ማካሄድ ይቻላል።

- መመሪያው ከሚፈቅደው የገንዘብ መጠን በላይ አስቀምጦ የተገኘን አካል #የጠቆመ ግለሰብ 15 በመቶ የወረታ ክፍያ ይከፈለዋል።

- በውጭ አገራት ገንዘብ ግብይት መፈጸምም ሆነ በህገወጥ መንገድ ይዞ መገኘት አይቻልም።

- ወርቅን በህገወጥ መልኩ ቤት ውስጥ ማከማቸት የማይቻል ሲሆን በህገወጥ መልኩ ወርቅን ያከማቸ ግለሰብ ለጠቆመ ግለሰብ ባንኩ በወቅቱ ባለው ግብይት የ15 በመቶ ወረታ ይከፈለዋል።

- በህገወጥ የሃዋላ የውጭ አገራት የተሰማሩ አካላትን ለጠቆመም እስከ 25 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል።

- በህገወጥ ገንዘብ ህትመት የተሰማሩ አካላትን ያጋለጠም ከ20 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል።

- ጠቋሚዎች ወረታውና ሽልማቱ የሚበረከትላቸው #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ነው።

Credit : ENA

@tikvahethiopia
👍1.17K👎34956😢32😱30🙏16🕊1