" የችግሩ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየከፋ ነው "
በአማራ ክልል ፣ በሰሜን ጎንደር 202 ሺህ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።
በዞኑ በተከሰተው ድርቅ 452 ሺ ዜጎች መጎዳታቸው ተገልጿል።
የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና የምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት ይፋ እንዳደረገው ፤ በዞኑ ከግንቦት አጋማሽ ጀምሮ በተከሰተው ድርቅ 452 ሺህ ዜጎች ተጎድተዋል፤ 202 ሺህ ዜጎችም አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፡፡
ከፅህፈት ቤቱ በተገኘው መረጃ ፦
- ጃናሞራ ፣ ጠለምት ፣ የበየዳ ወረዳዎችን ጨምሮ፣ ምሥራቅና ምዕራብ ጠለምትና የተወሰኑ የደባርቅ አካባቢዎች በድርቅ ተጎድተዋል፡፡
- ከግንቦት አጋማሽ ጀምሮ ዝናብ በወቅቱ ባለመዝነቡ ሳቢያ 6 ወረዳዎች ለድርቅ ተጋልጠዋል።
- በድርቁ ሳቢያ 19 ሺህ 500 ሄክታር ሰብል ጉዳት ደርሶበታል።
- በዝናብ እጥረት 103 ሺሕ እንስሳት ለድርቅ አደጋ የተጋለጡ ሲሆን 53 ሺሕ የሚደርሱ እንስሳት በድርቁ ሳቢያ #ሞተዋል።
- በጠለምትና ጃናሞራ ወረዳዎች በድርቁ ምክንያት ከ4 ሺሕ በላይ ዜጎች ከአካባቢያቸው ለቀው ወደ ወረዳ ማዕከላት ሄደዋል።
- ዞኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ድጋፍ ለማቅረብ ጥረት በማድረግ ላይ ነው ብለዋል፡፡
- በድርቁ አካባቢዎች ላይ ተላላፊ በሽታዎች በተለይም #የኮሌራ_በሽታ ተከስቷል።
- ድርቁ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ ለሚገኙ ዜጎች አስቸኳይ የዕለት ምግብ፣ መድኃኒቶች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ውሃና የእንስሳት መኖ ድጋፍ አስፈላጊ ነው።
- የችግሩ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየከፋ ነው። በድርቁ ሳቢያ ዜጎች ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ ሁሉም አካላት እንዲረባረቡ ፤ መንግሥት፣ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች፣ አጋር አካላት የተለያዩ ድጋፎችን እንዲያቀርቡ መልዕክት ተላልፏል።
እስካሁን ምን ድጋፍ ተደረገ ? ፅ/ቤቱ ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ክልሉ ከአንድ ሺሕ 500 ኩንታል በላይ የምግብ ድጋፍ ማድረጉንና ድጋፉን 14 ሺሕ ዜጎች ማድረስ እንደተቻለ ገልጿል።
Via EPA
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል ፣ በሰሜን ጎንደር 202 ሺህ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል።
በዞኑ በተከሰተው ድርቅ 452 ሺ ዜጎች መጎዳታቸው ተገልጿል።
የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና የምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት ይፋ እንዳደረገው ፤ በዞኑ ከግንቦት አጋማሽ ጀምሮ በተከሰተው ድርቅ 452 ሺህ ዜጎች ተጎድተዋል፤ 202 ሺህ ዜጎችም አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፡፡
ከፅህፈት ቤቱ በተገኘው መረጃ ፦
- ጃናሞራ ፣ ጠለምት ፣ የበየዳ ወረዳዎችን ጨምሮ፣ ምሥራቅና ምዕራብ ጠለምትና የተወሰኑ የደባርቅ አካባቢዎች በድርቅ ተጎድተዋል፡፡
- ከግንቦት አጋማሽ ጀምሮ ዝናብ በወቅቱ ባለመዝነቡ ሳቢያ 6 ወረዳዎች ለድርቅ ተጋልጠዋል።
- በድርቁ ሳቢያ 19 ሺህ 500 ሄክታር ሰብል ጉዳት ደርሶበታል።
- በዝናብ እጥረት 103 ሺሕ እንስሳት ለድርቅ አደጋ የተጋለጡ ሲሆን 53 ሺሕ የሚደርሱ እንስሳት በድርቁ ሳቢያ #ሞተዋል።
- በጠለምትና ጃናሞራ ወረዳዎች በድርቁ ምክንያት ከ4 ሺሕ በላይ ዜጎች ከአካባቢያቸው ለቀው ወደ ወረዳ ማዕከላት ሄደዋል።
- ዞኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ድጋፍ ለማቅረብ ጥረት በማድረግ ላይ ነው ብለዋል፡፡
- በድርቁ አካባቢዎች ላይ ተላላፊ በሽታዎች በተለይም #የኮሌራ_በሽታ ተከስቷል።
- ድርቁ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ላይ ለሚገኙ ዜጎች አስቸኳይ የዕለት ምግብ፣ መድኃኒቶች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ ውሃና የእንስሳት መኖ ድጋፍ አስፈላጊ ነው።
- የችግሩ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየከፋ ነው። በድርቁ ሳቢያ ዜጎች ለከፋ ችግር እየተጋለጡ በመሆኑ ሁሉም አካላት እንዲረባረቡ ፤ መንግሥት፣ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች፣ አጋር አካላት የተለያዩ ድጋፎችን እንዲያቀርቡ መልዕክት ተላልፏል።
እስካሁን ምን ድጋፍ ተደረገ ? ፅ/ቤቱ ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ክልሉ ከአንድ ሺሕ 500 ኩንታል በላይ የምግብ ድጋፍ ማድረጉንና ድጋፉን 14 ሺሕ ዜጎች ማድረስ እንደተቻለ ገልጿል።
Via EPA
@tikvahethiopia
😢691❤78🕊23🙏22😡17🥰14😱4
#ናይጄሪያ
ናይጄሪያ ውስጥ አንድ ባለሃብት ገንዘብ ለማደል በጠራበት ዝግጅት ላይ በተፈጠረ ግርግር አንዲት የ8 ዓመት ሕፃንን ጨምሮ 7 ሰዎች ተረጋግጠው እንደ #ሞቱ ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
ትላንትና እሁድ አልሃጂ ያኩቡ የተባለ ባለሀብት በሰሜን ምሥራቅ የባውቺ ግዛት ነዋሪዎች ወደ ቢሮው ከመጡ ለእያንዳንዳቸው 5 ሺህ ናይራ (የናይጄሪያ ገንዘብ) ለመስጠት ቃል ይገባል።
5 ሺህ ናይራ ወደ ዶላር ሲመነዘር 3 ዶላር ከ70 ሳንቲም ሲሆን፣ ወደ ብር ሲቀየር 210 ነው።
የባለሀብቱን የገንዘብ እደላ ጥሪ ተከተሎ በርካታ ሰዎች ይወጣሉ በዚህ ወቅት በተፈጠረ ግርግር ዕድሜያቸው ከ8 እስከ 55 የሚሆን 7 ሰዎች መሞታቸውን ፖሊስ አረጋግጧል።
ነዋሪዎች ግን የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከተጠቀሰው ይበልጣል ብለዋል።
ብዙ ጊዜ እንዲህ ያለ እደላ/እርዳታ ላይ ወንዶች የእርዳታ ገንዘብ ሲቀበሉ መታየት ስለማይፈልጉ ሴቶችን እንደሚልኩ ተነግሯል።
የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በዕለቱ የተፈጠረውን ነገር ለማጣራት ምርመራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
ቢሮው አካባቢ የጥሬ ገንዘብ ልገሳ ያሰናዳው ባለሀብቱ አልሃጂ ያኩቡ ማይሻኑ እስካሁን ያለው ነገር የለም።
የናይጄሪያ የምጣኔ ሀብት #መላሸቁን ተከትሎ በርካቶች እርዳታ ጠባቂ ሆነዋል። 5 ሺህ ናይራ አንድን ቤተሰብ ለአንድ ቀን መመገብ ይችላል።
ባለፈው ሳምንት በማዕከላዊ ናይጄሪያ የናሳራዋ ግዛት ዩኒቨርሲቲ ሩዝ ሲታደል ለመቀበል የወጡ የተወሰኑ #ተማሪዎች ተረጋግጠው #ሞተዋል።
ባለፈው ወር የናይጄሪያ ገቢዎች አገልግሎት ሩዝ በቅናሽ ዋጋ ሲሸጥ በተፈጠረ ግርግር የተወሰኑ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው አሳውቆ ነበር።
ናይጄሪያ ውስጥ ባለው የኑሮ ውድነት ምክንያት በርካቶች የሚቀበሉት ደመወዝ ከወር ወር ሊያደርሳቸው እንዳልቻለ ቢቢሲ አስነብቧል።
Via https://tttttt.me/thiqahEth
@tikvahethiopia
ናይጄሪያ ውስጥ አንድ ባለሃብት ገንዘብ ለማደል በጠራበት ዝግጅት ላይ በተፈጠረ ግርግር አንዲት የ8 ዓመት ሕፃንን ጨምሮ 7 ሰዎች ተረጋግጠው እንደ #ሞቱ ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
ትላንትና እሁድ አልሃጂ ያኩቡ የተባለ ባለሀብት በሰሜን ምሥራቅ የባውቺ ግዛት ነዋሪዎች ወደ ቢሮው ከመጡ ለእያንዳንዳቸው 5 ሺህ ናይራ (የናይጄሪያ ገንዘብ) ለመስጠት ቃል ይገባል።
5 ሺህ ናይራ ወደ ዶላር ሲመነዘር 3 ዶላር ከ70 ሳንቲም ሲሆን፣ ወደ ብር ሲቀየር 210 ነው።
የባለሀብቱን የገንዘብ እደላ ጥሪ ተከተሎ በርካታ ሰዎች ይወጣሉ በዚህ ወቅት በተፈጠረ ግርግር ዕድሜያቸው ከ8 እስከ 55 የሚሆን 7 ሰዎች መሞታቸውን ፖሊስ አረጋግጧል።
ነዋሪዎች ግን የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከተጠቀሰው ይበልጣል ብለዋል።
ብዙ ጊዜ እንዲህ ያለ እደላ/እርዳታ ላይ ወንዶች የእርዳታ ገንዘብ ሲቀበሉ መታየት ስለማይፈልጉ ሴቶችን እንደሚልኩ ተነግሯል።
የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በዕለቱ የተፈጠረውን ነገር ለማጣራት ምርመራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
ቢሮው አካባቢ የጥሬ ገንዘብ ልገሳ ያሰናዳው ባለሀብቱ አልሃጂ ያኩቡ ማይሻኑ እስካሁን ያለው ነገር የለም።
የናይጄሪያ የምጣኔ ሀብት #መላሸቁን ተከትሎ በርካቶች እርዳታ ጠባቂ ሆነዋል። 5 ሺህ ናይራ አንድን ቤተሰብ ለአንድ ቀን መመገብ ይችላል።
ባለፈው ሳምንት በማዕከላዊ ናይጄሪያ የናሳራዋ ግዛት ዩኒቨርሲቲ ሩዝ ሲታደል ለመቀበል የወጡ የተወሰኑ #ተማሪዎች ተረጋግጠው #ሞተዋል።
ባለፈው ወር የናይጄሪያ ገቢዎች አገልግሎት ሩዝ በቅናሽ ዋጋ ሲሸጥ በተፈጠረ ግርግር የተወሰኑ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው አሳውቆ ነበር።
ናይጄሪያ ውስጥ ባለው የኑሮ ውድነት ምክንያት በርካቶች የሚቀበሉት ደመወዝ ከወር ወር ሊያደርሳቸው እንዳልቻለ ቢቢሲ አስነብቧል።
Via https://tttttt.me/thiqahEth
@tikvahethiopia
😭1.16K❤130😢66😱65😡40🕊32🤔23🙏16👏10🥰8
#ጥንቃቄ🚨
" በተጣሉ ተተኳሾች እና ፈንጂዎች 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል " - የቆላ ተምቤን ወረዳ
በትግራይ ማእከላይ ዞን የቆላ ተምቤን ወረዳ በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ተተካሾች እና ፍንጂዎች ይገኛሉ።
እጅግ አስከፊውና ደም አፋሳሹን ጦርነት ተከትሎ በአከባቢው የተቀበሩትና የተጣሉት ተተካሾችና ፈንጂዎች በበርካታ ሰዎችና እንስሳት ላይ የሞትና የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ላይ እንደሆኑ ተነግሯል።
በወረዳው በተቀበሩትና በተጣሉት ተተኳሾችና ፈንጂዎች እስካሁን 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል።
አሁን ላይ አደጋውን ለመቀነስ ነዊና ጉያ በተባሉ የቀበሌ አስተዳደሮች በባለሙያዎች የተደገፈ የማምከን ስራ መጀመሩን የወረዳው አስተዳደር አሳውዋል።
ህዝቡ በአከባቢው ከተለመደው የተለየ ብረት ሲያገኝ ከመንካት እና ከመቀጥቀጥ ተቆጥቦ ለጸጥታ አካላት እንዲያሳውቅ ማሳሰቢያ ተለልፏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቆላ ተምቤን ወረዳ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ነው ያገኘው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" በተጣሉ ተተኳሾች እና ፈንጂዎች 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል " - የቆላ ተምቤን ወረዳ
በትግራይ ማእከላይ ዞን የቆላ ተምቤን ወረዳ በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ተተካሾች እና ፍንጂዎች ይገኛሉ።
እጅግ አስከፊውና ደም አፋሳሹን ጦርነት ተከትሎ በአከባቢው የተቀበሩትና የተጣሉት ተተካሾችና ፈንጂዎች በበርካታ ሰዎችና እንስሳት ላይ የሞትና የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ላይ እንደሆኑ ተነግሯል።
በወረዳው በተቀበሩትና በተጣሉት ተተኳሾችና ፈንጂዎች እስካሁን 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል።
አሁን ላይ አደጋውን ለመቀነስ ነዊና ጉያ በተባሉ የቀበሌ አስተዳደሮች በባለሙያዎች የተደገፈ የማምከን ስራ መጀመሩን የወረዳው አስተዳደር አሳውዋል።
ህዝቡ በአከባቢው ከተለመደው የተለየ ብረት ሲያገኝ ከመንካት እና ከመቀጥቀጥ ተቆጥቦ ለጸጥታ አካላት እንዲያሳውቅ ማሳሰቢያ ተለልፏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቆላ ተምቤን ወረዳ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ነው ያገኘው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
😭674❤92😢38🕊38🙏32😱17👏13😡13🤔10🥰7