TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

" የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ጥንቃቄ አድርጉ " - የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

በአዲስ አበባ ከተማ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ሁለት ሰዎች #በጎርፍ ተወስደው ህይወታቸው አለፈ።

ትላንት ምሽት 3:00  ሰዓት ጀምሮ ሲጥል የነበረዉን ዝናብ ተከትሎ በተፈጠረ ጎርፍ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ዳርፉር ወንዝ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሁለት ሴቶች በጎርፍ ተወስደዋል።

ይህን ተከትሎ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና ጠላቂ ዋናተኞች ፍለጋ ሲያካሂዱ ቆይተው ዕድሜያቸዉ 18 ዓመት የሆኑ ሁለት ሴቶችን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ከተለያየ ቦታ ማግኘት ችለዋል።

የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ኑሮአቸዉን እና እንቅስቃሴያቸዉን ወንዝ አካባቢ ያደረጉ ሁሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግና ከአካባቢዉ እንዲርቁ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።

@tikvahethiopia
😢1.22K👍44586🕊43😱41🥰12👎6🙏6