#AddisAbaba
" የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ጥንቃቄ አድርጉ " - የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
በአዲስ አበባ ከተማ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ሁለት ሰዎች #በጎርፍ ተወስደው ህይወታቸው አለፈ።
ትላንት ምሽት 3:00 ሰዓት ጀምሮ ሲጥል የነበረዉን ዝናብ ተከትሎ በተፈጠረ ጎርፍ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ዳርፉር ወንዝ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሁለት ሴቶች በጎርፍ ተወስደዋል።
ይህን ተከትሎ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና ጠላቂ ዋናተኞች ፍለጋ ሲያካሂዱ ቆይተው ዕድሜያቸዉ 18 ዓመት የሆኑ ሁለት ሴቶችን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ከተለያየ ቦታ ማግኘት ችለዋል።
የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ኑሮአቸዉን እና እንቅስቃሴያቸዉን ወንዝ አካባቢ ያደረጉ ሁሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግና ከአካባቢዉ እንዲርቁ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።
@tikvahethiopia
" የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ጥንቃቄ አድርጉ " - የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
በአዲስ አበባ ከተማ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ሁለት ሰዎች #በጎርፍ ተወስደው ህይወታቸው አለፈ።
ትላንት ምሽት 3:00 ሰዓት ጀምሮ ሲጥል የነበረዉን ዝናብ ተከትሎ በተፈጠረ ጎርፍ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ዳርፉር ወንዝ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሁለት ሴቶች በጎርፍ ተወስደዋል።
ይህን ተከትሎ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና ጠላቂ ዋናተኞች ፍለጋ ሲያካሂዱ ቆይተው ዕድሜያቸዉ 18 ዓመት የሆኑ ሁለት ሴቶችን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ከተለያየ ቦታ ማግኘት ችለዋል።
የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ኑሮአቸዉን እና እንቅስቃሴያቸዉን ወንዝ አካባቢ ያደረጉ ሁሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግና ከአካባቢዉ እንዲርቁ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።
@tikvahethiopia
😢1.22K👍445❤86🕊43😱41🥰12👎6🙏6