TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
'የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታችሁን ተከታተሉ'

ከምርጫ ጋር በተገናኘ ትላትን የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለ @tikvahuniversity እንዳሳወቀው የዩኒቨርሲቱ ተማሪዎች በምን መልኩ በምርጫ ይሳተፉ ? በሚለው ላይ እስካሁን በሚኒስቴሩ ደረጃ ምንም የተወሰነ ውሳኔ የለም።

ነገር ግን የተለያዩ ኒቨርሲቲዎች በውስጥ ማስታወቂያ ከምርጫው በፊት 1 ሳምንት ከምርጫው በኃላ 1 ሳምንት ተማሪዎቻቸውን እንደሚበቱ እያሳወቁ ይገኛሉ።

ሌሎች ደግሞ በውስጥ ማስታወቂያቸው "ከምርጫው በፊት ተማሪዎች ይበተናሉ" ስለሚባለው ጉዳይ የሚያውቁት ነገር እንደለ እንዲሁም የሚናፈሰው መረጃም ውሸት እንደሆነ በመግለፅ ተማሪዎች ተረጋግተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እያሳበቡ ይገኛሉ።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሆናችሁ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ተማሪዎች በምን መልኩ ነው በምርጫው የሚሳተፉት ? ለሚለው ጉዳይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ መረጃ ሲላክልን የምናሳውቃችሁ ይሆናል።

እስከዚያው ግን በተለያዩ የቴሌግራም ቻናሎች ላይ ሆነ የፌስቡክ ገፆች ላይ የሚወጡትን የተለያዩ መረጃዎች በመቀባበል ሳትረበሹ #በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታችሁን እየቀጠላችሁ ይፋዊ የሆነውን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ትጠብቁ ዘንድ አደራ እንላለን።

አዲስ የዩኒቨርሲቲ ተመዳቢ ተማሪዎች በተመለከተ አስፈላጊውን መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት በጠየቅ እናሳውቃለን። በተጨማሪም የ2013 ሀገር አቀፍ ፈተና ሂደትን ከትምህርት ሚኒስቴር ጠይቀን እናሳውቃለን።

ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባሉበርካታ የተጣረሱ መረጃዎች እንዳትደናገሩ።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#ምርጫ2013

በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ፦

- የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ መዘግየት ፣
- በድምፅ አሰጣጥ ላይ የሚታይ መደነጋገር፣
- ሰዓት አለማክበር፣
- የኮቪድ-19 ፕሮቶኮል አለመጠበቅ፣
- ረጃጅም ሰልፎች (በፍጥነት አለመሄድ) ፣
- የሰልፍ ተራ አለመጠበቅ፣
- የምርጫ ቁሳቁስ መቀያየር
- ቀልጥፍ ያለ መስተንግዶ ክፍተት
- መራጮች ምርጫ ካርዳቸውን የወሰዱበትን መታወቂያ ሳይዙ መሄድ
- "እከሌን ምረጡ" የሚል ቅስቀሳ ለማድረግ መሞከር የመሳሰሉት ችግሮች ከመስተዋላቸው በዘለለ የምርጫ ሂደቱ #በሰላም እየተካሄድ መሆኑን ከአዲስ አበባና ከክልል የምርጫ ጣቢያዎች የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።

የ Tikvah - Ethiopia አባላት በተመለከቷቸው የምርጫ ጣቢያዎች እድሜያቸው የገፋ ዜጎች ፣ እናቶች አባቶች ድምፅ ለመስጠት ተሰልፈው ተመልከተዋል። ነፍሠ ጡሮች፣ ልጅ የታቀፉ እናቶች ተሰልፈው ድምፅ ሲሰጡ አስተውለዋል።

በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ በፀጥታ እና በሰላም ረገድ ምንም ጥቆማ ከአባላቶቻችን አልተላከም፤ ሁሉም ሂደት #በተረጋጋ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገልፀውልናል።

Photo Credit : Tikvah Family (Addis Ababa)

@tikvahethiopia