TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር ካለፉት ሳምንታት ጀምሮ መንግስት ከTPLF ጋር ድርድር ሊያደርግ እንደሆነ የተለያዩ ምንጫቸው በግልፅ ያልተገለፁ/ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ሲወጡ ነበር። ዛሬ ከህ/ተ/ም/ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ድርድርን በተመለከተ መረጃ ሰጥተዋል። " ከማንም ጋር ሰላም ነው የምንፈልገው። " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " እያንዳንዷ የሰላም ቀን ለእኛ ትርፍ ታስገኝልናለች።…
#ድርድር
የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት በሰላም መቋጫ ያገኝ ዘንድ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ይታወቃል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህም አንዳንድ የውጭ ሀገር ሚዲያዎች ድርድርን በተመለከተ በግልፅ ምንጫቸው የማይታወቁ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ከርመዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ንግግር አለመጀመሩን ነገር ግን ለዚሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁሟል።
ትላንት ፓርላማ የቀረቡት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ የታወቀ አጥኚ ኮሚቴ ተቋቁሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት እየተመራ መሆኑን፤ እስካሁን ውጤቱን አለማሳወቁን እና የሚደራደረው ኮሚቴም ይሄ መሆኑን ጠቁመው ነበር። ድርድር ሲጀመር መንግስት የሚደብቀው ነገር እንደሌለም ገልፀው ነበር።
ይህ የጠቅላይ ሚስትሩ ንግግር ከተሰማ ብዙም ሳይቆይ በህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የተፃፈ ደብዳቤ ተሰራጭቷል።
ይኸው ደብዳቤ ህወሓት በኬንያ መንግስት በተጠራ ድርድር የሚሳተፍ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለመላክ መዘጋጀቱን ይገልጻል።
ደብዳቤው በኬንያ መንግስት የተጠራ ድርድር #በናይሮቢ ስለመኖሩ ፍንጭ የሰጠ ነው።
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሰላም ድርድሮችን በማስመልከት የትግራይ ክልልን አቋምን ለማሳወቅ ደብዳቤውን የፃፉት ለአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀ መንበርና የሴናጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል፣ ለኬንያው ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ፣ ለተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ ሞሃመድ ቢን ዛይድ አልናህያን እና ለታንዛኒያዋ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን እንዲሁም የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ነው።
ያንብቡ ; https://telegra.ph/Dr-Debretsion-GMicahel-06-15
@tikvahethiopia
የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት በሰላም መቋጫ ያገኝ ዘንድ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ይታወቃል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህም አንዳንድ የውጭ ሀገር ሚዲያዎች ድርድርን በተመለከተ በግልፅ ምንጫቸው የማይታወቁ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ከርመዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ንግግር አለመጀመሩን ነገር ግን ለዚሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁሟል።
ትላንት ፓርላማ የቀረቡት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ የታወቀ አጥኚ ኮሚቴ ተቋቁሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት እየተመራ መሆኑን፤ እስካሁን ውጤቱን አለማሳወቁን እና የሚደራደረው ኮሚቴም ይሄ መሆኑን ጠቁመው ነበር። ድርድር ሲጀመር መንግስት የሚደብቀው ነገር እንደሌለም ገልፀው ነበር።
ይህ የጠቅላይ ሚስትሩ ንግግር ከተሰማ ብዙም ሳይቆይ በህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የተፃፈ ደብዳቤ ተሰራጭቷል።
ይኸው ደብዳቤ ህወሓት በኬንያ መንግስት በተጠራ ድርድር የሚሳተፍ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ለመላክ መዘጋጀቱን ይገልጻል።
ደብዳቤው በኬንያ መንግስት የተጠራ ድርድር #በናይሮቢ ስለመኖሩ ፍንጭ የሰጠ ነው።
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሰላም ድርድሮችን በማስመልከት የትግራይ ክልልን አቋምን ለማሳወቅ ደብዳቤውን የፃፉት ለአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀ መንበርና የሴናጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል፣ ለኬንያው ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ፣ ለተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ ሞሃመድ ቢን ዛይድ አልናህያን እና ለታንዛኒያዋ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን እንዲሁም የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን ጨምሮ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ነው።
ያንብቡ ; https://telegra.ph/Dr-Debretsion-GMicahel-06-15
@tikvahethiopia
👍10