TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
* Confirmed በደቡብ አፍሪካ በነበረው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ድርድር ላይ ከብዙ ክርክሮች በኃላ በሁለቱም ወገኖች የተፈረመው የስምምነት ዝርዝር ሰነድ ከላይ የተያያዘው ነው። በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ስምምነቱ ከተፈረመ በኃላ የተለያዩ ስምምነቱን የሚገልፁ " Draft " ወረቀቶች ሲሰራጭ የነበር ቢሆንም ከሰላም ንግግሩ አመቻቾች (አፍሪካ ህብረት)፣ ከሰላም ንግግሩ ተሳታፊዎች…
የ ' ሰላም ስምምነቱ ' #ስኬታማ እንዲሆን ምን ይደረግ ?

የፕሪቶሪያው የ "ሰላም ስምምነት" ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ስምምነት የተደረሰባቸው ነጥቦች በአግባቡ መሬት ይዘው፤ ሲፈጸሙና የጦርነቱ ሰለባ የሆነው ሕዝብ እፎይታን ሲያገኝ እና ሲታከም ብቻ መሆኑን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት በላከል መግለጫ አሳውቋል።

ም/ ቤቱ የሰላም ስምምነቱ ፍሬያማ ይሆን ዘንድ ፦

- የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሓት በስምምነቱ ማእቀፍ ሊተገብሩ በተስማሙት ሠነድ መሠረት ፦ የአፈጻጸም ሂደቱ አካታች ፣ ተዓማኒ እና ግልጽ ሆኖ በታመለት ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ እንዲቻል በፍጹም ቁርጠኛነት እንዲሁም በተጠያቂነት መንፈስ እንዲያከናውኑ በአጽንዖት ጠይቋል።

- የፓለቲካ ኃይሎች ስምምነቱ ፍሬ እንዲያፈራና በሀገራችን ዘላቂ ልማትና እድገት እንዲኖር የሰላም ደጋፊ ሊሆኑ ይገባል ብሏል። የእልህ እና የብሽሽቅ ፕሮፖጋንዳዎች ቆመው የአሸናፊነትና ተሸናፊነት ኋላቀር አስተሳሰብ ሊወገዝ እንደሚገባው ገልጾ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን #በይቅርታ ሕመማችንን በጋራ እንድናክም ሲል ጥሪ አቅርቧል።

- የተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት እጅግ በጣም ውጤታማ ይሆን ዘንድ በጦርነቱ ሳቢያ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል ብሏል ፤ ለዚህም ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርቧል።

- በተደረገው የሰላም ስምምነት ስኬታማነት ላይ ስጋት ያላቸው ዜጎች ፣ ፖለቲከኞች ፣ አክቲቪስቶች ፣ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሌሎችም ኢትዮጵያ ከሰላም ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌላት በማወቅ ስለሰላም መልካሙን እንዲያስቡና እንዲያደርጉ አሳስቧል።

(ሙሉ የም/ቤቱ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
👍754🕊108👎6524🙏17😱9😢1