መልካም አዲስ ዓመት!
ውድ በዚህ ቤት #ሰውነትን አስቀድማችሁ የተሰባሰባችሁ የሀገራችን ልጆች እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
ሁላችን እንደምናስታውሰው 2013 በገባ በጥቂት ወራት በሀገራችን ጦርነት ተቀስቅሶ ደስታ የተሞላ፣ ሰላም የሰፈነበት፣ ብዙ እቅዶቻችን የምናሳካበት ብለን ያሰብነው ዓመት በጦርነት፣ ሰቆቃ፣ በዜጎች ሞት፣ በረሃብ፣ በጭንቀት፣በደህንነት ስጋት ተሞልቶ ተሰናብተነዋል።
በ2013 በጦርነት ምክንያት ቁጥራቸውን የማናውቃቸው ነገር ግን እጅግ በርካታ ዜጎቻችን ረግፈዋል፣ አንዳዶች እንደወጡ ቀርተዋል፣ ባላሰቡበት ተጨፍጭፈዋል፣ ሺዎች አካላቸው ጎድሏል፤ሴት እህቶቻችን ተደፍረዋል ተጠቅተዋል ሚሊዮኖች ተርበዋል ተጠምተዋል፣ሚሊዮኖች ከገዛ ቀያቸው ተፈናቅለው ተሰደዋል።
በትግራይ፣ አፋር፣ አማራ፣ ኦሮሚያ (ወለጋ)፣ ቤ/ጉሙዝ...ምንም ከጦርነት ጋር ንክኪ የሌላቸው፣ ስለሚሆነው ነገር ፍፅሞ የማያውቁ ንፁሃን ዜጎቻችን፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ህፃናት ከነተስፋቸው አሸልበዋል፤በወጡበት ቀርተዋል፤እናቶች ልጆቻቸውን አንጠልጥለው ተሰደዋል፣አባቶች አልቅሰዋል፣አንብተዋል።
በዓመቱ ወንድም እህቶቻችሁን ያጣችሁ፣ የምትወዱትን የተነጠቃችሁ፣ እናት አባቶች ፅናቱን ብርታቱን ይስጣችሁ። አሁንም በችግር ላይ ላሉ ወገኖቻችን ፈጣሪ ይድረስላቸው።
እንደአንድ ሀገር ዜጋ ይህን አዲስ አመት የምንቀበለው በፍፁም የስሜት መረበሽ ውስጥ ቢሆንም ፈጣሪ ሁሉን እንዲያቀናው እንማፀናለን።
ዓመቱ የሰላም፣ግጭትና ሰቆቃ የማንሰማትበት፣ ከጎናችን ማንም የማይጎድልበት እንዲሆን እንመኛለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤታችን፤ መሰብሰቢያችን ነው፤ በአዲሱ ዓመት ቤተሰባዊ ቅርርባችን ሚጠናከርባቸውን ሀሳቦች ለእናተ እንደምናቀርብ ከወዲሁ ቃል እንገባለን።
❤️ኢትዮጵያ እናታችን ተከብራ ትኑርልን❤️
@tikvahethiopia
ውድ በዚህ ቤት #ሰውነትን አስቀድማችሁ የተሰባሰባችሁ የሀገራችን ልጆች እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
ሁላችን እንደምናስታውሰው 2013 በገባ በጥቂት ወራት በሀገራችን ጦርነት ተቀስቅሶ ደስታ የተሞላ፣ ሰላም የሰፈነበት፣ ብዙ እቅዶቻችን የምናሳካበት ብለን ያሰብነው ዓመት በጦርነት፣ ሰቆቃ፣ በዜጎች ሞት፣ በረሃብ፣ በጭንቀት፣በደህንነት ስጋት ተሞልቶ ተሰናብተነዋል።
በ2013 በጦርነት ምክንያት ቁጥራቸውን የማናውቃቸው ነገር ግን እጅግ በርካታ ዜጎቻችን ረግፈዋል፣ አንዳዶች እንደወጡ ቀርተዋል፣ ባላሰቡበት ተጨፍጭፈዋል፣ ሺዎች አካላቸው ጎድሏል፤ሴት እህቶቻችን ተደፍረዋል ተጠቅተዋል ሚሊዮኖች ተርበዋል ተጠምተዋል፣ሚሊዮኖች ከገዛ ቀያቸው ተፈናቅለው ተሰደዋል።
በትግራይ፣ አፋር፣ አማራ፣ ኦሮሚያ (ወለጋ)፣ ቤ/ጉሙዝ...ምንም ከጦርነት ጋር ንክኪ የሌላቸው፣ ስለሚሆነው ነገር ፍፅሞ የማያውቁ ንፁሃን ዜጎቻችን፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ህፃናት ከነተስፋቸው አሸልበዋል፤በወጡበት ቀርተዋል፤እናቶች ልጆቻቸውን አንጠልጥለው ተሰደዋል፣አባቶች አልቅሰዋል፣አንብተዋል።
በዓመቱ ወንድም እህቶቻችሁን ያጣችሁ፣ የምትወዱትን የተነጠቃችሁ፣ እናት አባቶች ፅናቱን ብርታቱን ይስጣችሁ። አሁንም በችግር ላይ ላሉ ወገኖቻችን ፈጣሪ ይድረስላቸው።
እንደአንድ ሀገር ዜጋ ይህን አዲስ አመት የምንቀበለው በፍፁም የስሜት መረበሽ ውስጥ ቢሆንም ፈጣሪ ሁሉን እንዲያቀናው እንማፀናለን።
ዓመቱ የሰላም፣ግጭትና ሰቆቃ የማንሰማትበት፣ ከጎናችን ማንም የማይጎድልበት እንዲሆን እንመኛለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤታችን፤ መሰብሰቢያችን ነው፤ በአዲሱ ዓመት ቤተሰባዊ ቅርርባችን ሚጠናከርባቸውን ሀሳቦች ለእናተ እንደምናቀርብ ከወዲሁ ቃል እንገባለን።
❤️ኢትዮጵያ እናታችን ተከብራ ትኑርልን❤️
@tikvahethiopia
😢2