TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ቅዱስ ፓትርያርኩ የተመረጡትን አባቶችን አልሾምም አላሉም  ፤ ወደ ትግራይም በተያዘው መርሀግብር ይጓዛሉ " - ቤተክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ በአንዳንድ ማኅበራዊ  ሚዲያዎች ላይ " ቅዱስ ፓትርያርኩ በቅዱስ ሲኖዶስ የተመረጡትን መነኮሳት አልሾምም ፤ ወደ ትግራይም አልሔድም " ብለዋል  ተብሎ እየተሰራጨ ያለው ዜና ፍጹም ሐሰት ነው አለች።

ቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ፓትርያርኩ " የተመረጡትን አባቶችንም አልሾምም አላሉም። በተያዘው መርሐ ግብር  መሠረትም ወደ ትግራይ ይጓዛሉ " ስትል አሳውቃላች።

ቤተክርስቲያንኗ " እንዲህ ዓይነቱ ሆን ተብሎ የሚሰራጭ የሐሰት ዘገባ ፤ #የእርቅ ሂደቱን የማደናቀፍ እና  የቅዱስ ፓትርያርኩንስም በሐስት የማጠልሽት የተለመደና ቀጣይ የሐሰተኞችና ስም አጥፊዎች ዘመቻ አካል ነው " ያለች ሲሆን " ይህን አይነቱን የሐሰትና የፈጠራ ወሬ በቅድስት እርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነዙ  አካላትም ከዚህ ደርጊታቸው እንዲታቀቡ በጥብቅ እናሳስባለን " ብላለች።

@tikvahethiopia
👍1.17K👎149107🕊51🙏25🥰13😢7😱3