TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ተረጋግተን በጥንቃቄ ብናሽከረክር ምናለበት ?

" በአደጋው ከሞቱት ሦሥቱ የግብርና ባለሙያዎች የተቀሩት ነዋሪዎች ናቸው " - የስልጤ ዞን አስተዳደር

ትላንትና #ሀሙስ ጥዋት በስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ8 ወገኖቻችን ህይወት አልፏል።

አደጋው የደረሰው ከአዲስ አበባ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ወደ አርባ ምንጭ ሲጓዝ የነበረ ሀገር አቋራጭ አውቶቢስ ከቢለዋንጃ ወደ ሁልባራግ ኬራቴ ተሳፋሪዎችን ይዞ ሲጓዝ ከነበረ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪ/ባጃጅ በመጋጨቱ ነው።

የስልጤ ዞን አስተዳደር " በአደጋው ህይወታቸውን ካጡት ውስጥ ህዝብና መንግሥት የጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ደፋ ቀና የሚሉ ሦስት የግብርና ባለሙያዎች አሉበት ሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው
" ብሏል።

የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ፥ በባጃጅ ሲጓዙ የነበሩ 8 ተሳፋሪዎች በሙሉ ህይወታቸው ማለፉን ገልጾ " አደጋው ዘግናኝ  ነው " ብሎታል።

የሟቾቹ አስክሬን በመቆራረጡና በደም በመጨማለቁ ፊታቸውን በማጠብ ነው ማንነታቸውን መለየት የተቻለው።

ፖሊስ " ጉዳት አድራሹ አውቶብስ በከፍተኛ ፍጥነት ይሽከረከር እንደነበር መረጃዎች አሉ  ነገር ግን ተጨማሪ የማጣራት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ " ሲል ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ገልጿል።


@tikvahethiopia
😢478😭31976🕊27😱17🙏11🤔8😡6