የ "መ" ህጎች ተረት
ተረት ተረት......(የላም በረት)
ከዕለታት ባንዱ ቀን፣
ከህግጋት መሀል በ"መ"ሚጀምሩ፥
አንድ ላይ ሚጠሩ፣
ሶስቱ የ"መ"ህጎች፣
በሚባል ቤታቸው ይኖሩ ነበሩ።
መታቀብ፣መወ'ሰን፣መጠቀም፥
የበሽታን ጠጠር፣
ከምስር ለመልቀም፥
ሲኖሩ ሲኖሩ
ሲኖሩ......ሲኖሩ........
ለሚጠ'ቀሟቸው፣
በፈጠሯቸው አፍ፣ሰርክ ሲነገሩ፥
በነጋሪዎች ገላ፣
በሰሚው ጭን እሳት፣
አመድ ሆነው ቀሩ።
ትውልድ ሲገለገል፣በመቃብር ቤቱ፥
እንዲህ ተነበበ፣
በ'መታቀብ'ገዳይ፣
የ'መታቀብ' ሞቱ።
"መታቀብ"
"መታቀብ ተብዬው፣
የቅድመ-ጋብቻ፣ወሲብን ያግዳል፥
ህጉ እውን ከሆነ፣
ሰው ከማሕጸን ሲወጣ፣
ከመራቢያው ጋራ ለምን ይወለዳል?"
በሚል ፍልስፍና፥
መታቀብ ተሰዋች፣
በጭኖች ፍም-እሳት፣
ቃጠሎ ታፍና።
ትውልድ ሲገለገል፣በመቃብር ቤቱ፥
እንዲህ ተነበበ፣
በ"መወ'ሰን" ገዳይ፣
የ"መወሰ'ን" ሞቱ።
"መወ'ሰን"
"መወ'ስን ተብዬው፣
ካንድ በላይ አጋር፣
እንዳይኖር ያግባባል፥
ህጉ እውን ከሆነ፣
ከቅዱሱ ቃሉ ላይ፣
"ላለው ይጨመራል"
ለምን ይነበባል?"
ባላ'ቸው አንድ ላይ፣
ሌላን ለመጨመር፣ቃል እያጣቀሱ፥
በ"ቅዱስ ቃል" ቀሉት፣
ባንዲት ስንኝ ወጣ፣
የ"መወ'ሰን" ነፍሱ።
"መጠቀም"
የመጠቀም ህጉ ፣
"ኮንዶም"ን መጠቀም ፣
የሚለውን ያትታል፥
ግና ምን ያደርጋል
"ያገኙትን ዕድል
ባግባቡ መጠቀም"
በሚለው ተረቷል።
የ"መጠቀም" ህጉም-
ባንዳንዶች ሲነሳ፣
በሌሎች ይሞታል።
(ጭብጥ ሀሳብ)
የህግጋት መርቀቅ፣
ህጉን ያልወደደን እንደምን ይገዛል፥
እንደምን ይነካል፥
ህጉን ባልወደደው፣
በተገዢው ልኬት፣
ስፌቱ ተስፍቶ፣በህግጋት ይተካ'ል።
ስንታየሁ አዲሱ ሳንታ
(@San2w)
@Ezihbetsanaddis
ሚያዚያ 29/2011
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
@getem
@getem
@gebriel_19
ተረት ተረት......(የላም በረት)
ከዕለታት ባንዱ ቀን፣
ከህግጋት መሀል በ"መ"ሚጀምሩ፥
አንድ ላይ ሚጠሩ፣
ሶስቱ የ"መ"ህጎች፣
በሚባል ቤታቸው ይኖሩ ነበሩ።
መታቀብ፣መወ'ሰን፣መጠቀም፥
የበሽታን ጠጠር፣
ከምስር ለመልቀም፥
ሲኖሩ ሲኖሩ
ሲኖሩ......ሲኖሩ........
ለሚጠ'ቀሟቸው፣
በፈጠሯቸው አፍ፣ሰርክ ሲነገሩ፥
በነጋሪዎች ገላ፣
በሰሚው ጭን እሳት፣
አመድ ሆነው ቀሩ።
ትውልድ ሲገለገል፣በመቃብር ቤቱ፥
እንዲህ ተነበበ፣
በ'መታቀብ'ገዳይ፣
የ'መታቀብ' ሞቱ።
"መታቀብ"
"መታቀብ ተብዬው፣
የቅድመ-ጋብቻ፣ወሲብን ያግዳል፥
ህጉ እውን ከሆነ፣
ሰው ከማሕጸን ሲወጣ፣
ከመራቢያው ጋራ ለምን ይወለዳል?"
በሚል ፍልስፍና፥
መታቀብ ተሰዋች፣
በጭኖች ፍም-እሳት፣
ቃጠሎ ታፍና።
ትውልድ ሲገለገል፣በመቃብር ቤቱ፥
እንዲህ ተነበበ፣
በ"መወ'ሰን" ገዳይ፣
የ"መወሰ'ን" ሞቱ።
"መወ'ሰን"
"መወ'ስን ተብዬው፣
ካንድ በላይ አጋር፣
እንዳይኖር ያግባባል፥
ህጉ እውን ከሆነ፣
ከቅዱሱ ቃሉ ላይ፣
"ላለው ይጨመራል"
ለምን ይነበባል?"
ባላ'ቸው አንድ ላይ፣
ሌላን ለመጨመር፣ቃል እያጣቀሱ፥
በ"ቅዱስ ቃል" ቀሉት፣
ባንዲት ስንኝ ወጣ፣
የ"መወ'ሰን" ነፍሱ።
"መጠቀም"
የመጠቀም ህጉ ፣
"ኮንዶም"ን መጠቀም ፣
የሚለውን ያትታል፥
ግና ምን ያደርጋል
"ያገኙትን ዕድል
ባግባቡ መጠቀም"
በሚለው ተረቷል።
የ"መጠቀም" ህጉም-
ባንዳንዶች ሲነሳ፣
በሌሎች ይሞታል።
(ጭብጥ ሀሳብ)
የህግጋት መርቀቅ፣
ህጉን ያልወደደን እንደምን ይገዛል፥
እንደምን ይነካል፥
ህጉን ባልወደደው፣
በተገዢው ልኬት፣
ስፌቱ ተስፍቶ፣በህግጋት ይተካ'ል።
ስንታየሁ አዲሱ ሳንታ
(@San2w)
@Ezihbetsanaddis
ሚያዚያ 29/2011
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
@getem
@getem
@gebriel_19
እናትዬ
♥♥♥♥♥🔸▪
ምሣሣላት አለች አይቼ ማልጠግባት
አኑርልኝ እያልኩ ዘውትር ማነባላት
ከዕድሜ ግማሹን ተችሎ ብሰጣት
ቢያንስባት እንጂ እሷ አይበዛባት
ደስታዋን እያየሁ ደስታን እንዳገኝበት
ጌታ ሆይ አኑራት...
በመኖሯ ስላለ ..የኔ ሕይወት
እናቴ የኔ እናት.....
የሚገባሽ ነገር ምን ይሆን እላለሁ?
ላረግሽልኝ ሁሉ ልመልስ እሻለሁ
ከ9ወር ጀምሬ ማብቂያውን አጣለው
ውለታሽ ተቆጥሮ ከቃላት በላይ ነው
ፍቅርሽ እንዳይወዳደር ወደር እንኳ የለው
እና እናትዬ .....እስኪ ምን ላርግልሽ?
እኔ ፈልጌ አጣሁ.. ላንቺ ሚመጥንሽ፣
ወድሻለሁ ማለት መሰለኝ ሚያንስብሽ፣
መውደዴን በምን ..ልግለፅልሽ?
እናትዬ.....እስኪ ምን ላርግልሽ?
ውብ ቃላቶች ብደረድር...፣
አይችሉም ሊገልፁ ለሆንሽልኝ ነገር፣
እናቴ ምን ልናገር...፣
አጣሁ ቃል ፈልጌ ስላንቺ ልዘረዝር፣
ግን
ወድሻለሁ ማለት ከገለፀ ፍቅር፣
ወድሻለሁ ብዬ በቃል ብቻ አልቅር፣
የሚገባሽን ሁሉ ላሳይሽ በተግባር።
እናትዬ ..እስኪ ምን ላርግልሽ?
የሚመጥን ካለ.. ለውለታሽ ምላሽ
**ብሩክ ፍፁም
"መልካም የእናቶች ቀን "
@getem
@getem
@buraaye
♥♥♥♥♥🔸▪
ምሣሣላት አለች አይቼ ማልጠግባት
አኑርልኝ እያልኩ ዘውትር ማነባላት
ከዕድሜ ግማሹን ተችሎ ብሰጣት
ቢያንስባት እንጂ እሷ አይበዛባት
ደስታዋን እያየሁ ደስታን እንዳገኝበት
ጌታ ሆይ አኑራት...
በመኖሯ ስላለ ..የኔ ሕይወት
እናቴ የኔ እናት.....
የሚገባሽ ነገር ምን ይሆን እላለሁ?
ላረግሽልኝ ሁሉ ልመልስ እሻለሁ
ከ9ወር ጀምሬ ማብቂያውን አጣለው
ውለታሽ ተቆጥሮ ከቃላት በላይ ነው
ፍቅርሽ እንዳይወዳደር ወደር እንኳ የለው
እና እናትዬ .....እስኪ ምን ላርግልሽ?
እኔ ፈልጌ አጣሁ.. ላንቺ ሚመጥንሽ፣
ወድሻለሁ ማለት መሰለኝ ሚያንስብሽ፣
መውደዴን በምን ..ልግለፅልሽ?
እናትዬ.....እስኪ ምን ላርግልሽ?
ውብ ቃላቶች ብደረድር...፣
አይችሉም ሊገልፁ ለሆንሽልኝ ነገር፣
እናቴ ምን ልናገር...፣
አጣሁ ቃል ፈልጌ ስላንቺ ልዘረዝር፣
ግን
ወድሻለሁ ማለት ከገለፀ ፍቅር፣
ወድሻለሁ ብዬ በቃል ብቻ አልቅር፣
የሚገባሽን ሁሉ ላሳይሽ በተግባር።
እናትዬ ..እስኪ ምን ላርግልሽ?
የሚመጥን ካለ.. ለውለታሽ ምላሽ
**ብሩክ ፍፁም
"መልካም የእናቶች ቀን "
@getem
@getem
@buraaye
👍1
በነፍስና ስጋ
(በኤደን)
እኔ ያላንቺ ምንም ነኝ ያልኩትኝ
ባዶነቴ ታውቆኝ አንቺ የሞላሺኝ
ጥሩና መጥፎውን ደግና ክፉን
እንዳውቅልሽ ብለሽ
እያወራሽ ሳይሆን ተግብረሽ ያሳየሽ
አንቺ ማለት ለኔ ምርጧ እ-ናቴ ነሽ
........:... .....::::::::::
ሠው እንዴት ሞትን ሞቶ ያሳየኛል
ምንም ሳይለቀስ ነፍስሽ ሳትወጣ
ጥቁር ሳይለበስ
ትንፋስሽም ሳይቆም
በህይወት እያለሽ
እየሄደ እግርሽ
እኔን ለማኖር ነው
።።።።።።።።።።።።።።።።
በጠቆረው አለም እሳት በበዛበት
በየቦታው እሾህ ጉድጓድ በሞላበት
እንቅፋት ባለበት
ብዙ ግዜ ሞተሽ ፈጣሪ እያነሳሽ
አይዞሽ ባይ ሳይኖርሽ
ከመጠን ሳይቆጥሩሽ
ረግጠው አልፈውሽ
የህይወት ሞት ሞተሽ
ለኔ ለተራዋ ልብ ላጣች ልጅሽ
በሞትሽ እያኖርሽ
።።።።።።።።።።።።።።።
አንቺ ማለት እ-ማ
ብርቄ ድንቄ ልቤ አይኔ
ሁሉ ነገሬ ነሽ
ከሌለሽ የሌለዉ
ሲደክምሽ የምሞት
በሞተው ህይወትሽ
እየተረማመድኩ
ወደራሴ ስኬት
ወደፊት እየሄድኩ
በነፍስ ብትለይኝ
ቁልቁል ተምዘግዝጌ
አጥንቴ ማይገኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።
እኔ ማለት ያንቺ ስሪት ነኝ
የሞትሽም ሟች ነኝ
በሞትሽ ውስጥ ህይወት ያለኝ
@getem
@getem
@gebriel_19
(በኤደን)
እኔ ያላንቺ ምንም ነኝ ያልኩትኝ
ባዶነቴ ታውቆኝ አንቺ የሞላሺኝ
ጥሩና መጥፎውን ደግና ክፉን
እንዳውቅልሽ ብለሽ
እያወራሽ ሳይሆን ተግብረሽ ያሳየሽ
አንቺ ማለት ለኔ ምርጧ እ-ናቴ ነሽ
........:... .....::::::::::
ሠው እንዴት ሞትን ሞቶ ያሳየኛል
ምንም ሳይለቀስ ነፍስሽ ሳትወጣ
ጥቁር ሳይለበስ
ትንፋስሽም ሳይቆም
በህይወት እያለሽ
እየሄደ እግርሽ
እኔን ለማኖር ነው
።።።።።።።።።።።።።።።።
በጠቆረው አለም እሳት በበዛበት
በየቦታው እሾህ ጉድጓድ በሞላበት
እንቅፋት ባለበት
ብዙ ግዜ ሞተሽ ፈጣሪ እያነሳሽ
አይዞሽ ባይ ሳይኖርሽ
ከመጠን ሳይቆጥሩሽ
ረግጠው አልፈውሽ
የህይወት ሞት ሞተሽ
ለኔ ለተራዋ ልብ ላጣች ልጅሽ
በሞትሽ እያኖርሽ
።።።።።።።።።።።።።።።
አንቺ ማለት እ-ማ
ብርቄ ድንቄ ልቤ አይኔ
ሁሉ ነገሬ ነሽ
ከሌለሽ የሌለዉ
ሲደክምሽ የምሞት
በሞተው ህይወትሽ
እየተረማመድኩ
ወደራሴ ስኬት
ወደፊት እየሄድኩ
በነፍስ ብትለይኝ
ቁልቁል ተምዘግዝጌ
አጥንቴ ማይገኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።
እኔ ማለት ያንቺ ስሪት ነኝ
የሞትሽም ሟች ነኝ
በሞትሽ ውስጥ ህይወት ያለኝ
@getem
@getem
@gebriel_19
እናት
(ቡሩክ ካሳሁን)
እማ
ከመውደዶች ህንፃ ከፍቅሮች ከተማ
የተገነባሽው የማትፈርሽ ሀገር
የማትበታተኝ እፁብ ድንቅ ነገር
የቴውድሮስ ውጥን አስቀድሞ የገባሽ
አንቺ አንድ ሆነሽ ብዙውን ያግባባሽ
.
በአለም ኑሪ ከፍ ብለሽ እንደ ማማ…
የሰላም የተስፋ የርህራሄ አርማ
በውስጥሽ ለሚኖር የአናብስት ግርማ
ምድርን አንቀጥቅጦ ሰማትን ፈልጦ
ለሚገዛ ንጉስ ድንበርን አቋርጦ
ዙፋን እና መንበር ቀድመሽ የምትሆኚ
ለልጅሽ ፍስሀን ደስታን ምትመኚ
.
እናት
በአለም ኑሪ ከፍ ብለሽ እንደ ማማ
ዘእንበለ ድካም ወፃማ
ካንቺ ልግባባ እንጂ ካለም አልስማማ
አንቺን ከሚወስዱ ህይወቴን ልቀማ
እንዳሻቸው ሁሉ ከቤቴ ያስወጡኝ
ያለኝን ሀብት ንብረት ሁሉንም ይንጠቁኝ ሁሉንም ያሳጡኝ
ካንቺ አይነጥሉኝ በዚህ ሁሉ ግና
እንዳቺ የሚሆን ከቶ የለምና፡፡
05/09/2007 ዓ.ም
@getem
@getem
@burukassahunC
(ቡሩክ ካሳሁን)
እማ
ከመውደዶች ህንፃ ከፍቅሮች ከተማ
የተገነባሽው የማትፈርሽ ሀገር
የማትበታተኝ እፁብ ድንቅ ነገር
የቴውድሮስ ውጥን አስቀድሞ የገባሽ
አንቺ አንድ ሆነሽ ብዙውን ያግባባሽ
.
በአለም ኑሪ ከፍ ብለሽ እንደ ማማ…
የሰላም የተስፋ የርህራሄ አርማ
በውስጥሽ ለሚኖር የአናብስት ግርማ
ምድርን አንቀጥቅጦ ሰማትን ፈልጦ
ለሚገዛ ንጉስ ድንበርን አቋርጦ
ዙፋን እና መንበር ቀድመሽ የምትሆኚ
ለልጅሽ ፍስሀን ደስታን ምትመኚ
.
እናት
በአለም ኑሪ ከፍ ብለሽ እንደ ማማ
ዘእንበለ ድካም ወፃማ
ካንቺ ልግባባ እንጂ ካለም አልስማማ
አንቺን ከሚወስዱ ህይወቴን ልቀማ
እንዳሻቸው ሁሉ ከቤቴ ያስወጡኝ
ያለኝን ሀብት ንብረት ሁሉንም ይንጠቁኝ ሁሉንም ያሳጡኝ
ካንቺ አይነጥሉኝ በዚህ ሁሉ ግና
እንዳቺ የሚሆን ከቶ የለምና፡፡
05/09/2007 ዓ.ም
@getem
@getem
@burukassahunC
አቤቱ ህዝብህን አድን
መጣሁኝ ብለክ እንደሄድክ
ይመጣል ብለን በተስፋ
ደጃፉ ገርበብ እንዳለ
በራፉን በቅጥ ሳንዘጋ
ምፃትህ ቢዘገይ ጊዜ
ተስፋችን እየሰለለ
ስንቱ አሳች ወደ ውስጥ ገባ
ስንቱስ ነው የኮበለለ።
አቤቱ ህዝብህን አድን
ከክፉም አንተ ጠብቀው
መምጫክን ወይ ሹክ በለው
ወይ ና ና በሩን ቀርቅረው ።
* * * * * * *
በስሜ ሺ ይነሳሉ
የምትል ቃልህ ቀን ነስታ
እነሆኝ እልፎች አምታቱን
ሰብለ አዳም ግራ ተጋባ።
ለስምህ ታርጋ ለጥፈው
አርገውክ ምርጫ ቅስቀሳ
ለምስልህ ዋጋ ተምነው
ሆንክብን ነፃ ጨረታ።
አቤቱ እርስትህን ባርክ ....
በምርጫው ወይ ተሸንፈን
ወይ አጥተን ሳንገዛህ ብንቀር
ብይንህ ሚዛኑን ስቶ
በፍርድህ ከምንማረር
እዚህ ነኝ የሚል ምልክት
እባክህ ከደጅህ አኑር።
* * * * * * *
ስንፀድቅ ቤታችን ጋብዘን
ስናፅ ከሰማይ ሰቅለን
ስንዘፍን ሶስትዜ አማትበን
ስንገድል እሱ ያቃል ብለን
ስንሰርቅ የግዜር ስጦታ
ስንዘሙት በግዜር ሰላምታ
አንተኑ ባንተው አፍርሰን
ሌላ ግዜር እኛው አብጅተን
ስትመጣ መልክህ ባይለየን
ሗላ ላይ እንዳታዝንብን።
አቤቱ ህዝብህን አድን.....
.... ከክፉም አንተው ጠብቀን
ፅድቅና ኩነኔ መሀል
ያኖርከው ቀጭኑ መስመር ከድፍረት ከእምነት ማጣት
ደብዝዞ ከመደናበር
እንዳሻን እየሰረዝን
እንዳሻን ከምናሰምረው
አቤቱ ፈጣሪያችን ሆይ
ቅፅሩን በግንብ አድርገው።
* * *
አቤቱ ወዴት ቆመሀል
ዝምታህ ከአውራ መብረቅ
ግርማው እጅግ ያስፈራል።
* * *
ዳኒ.B
@getem
@getem
@gebriel_19
መጣሁኝ ብለክ እንደሄድክ
ይመጣል ብለን በተስፋ
ደጃፉ ገርበብ እንዳለ
በራፉን በቅጥ ሳንዘጋ
ምፃትህ ቢዘገይ ጊዜ
ተስፋችን እየሰለለ
ስንቱ አሳች ወደ ውስጥ ገባ
ስንቱስ ነው የኮበለለ።
አቤቱ ህዝብህን አድን
ከክፉም አንተ ጠብቀው
መምጫክን ወይ ሹክ በለው
ወይ ና ና በሩን ቀርቅረው ።
* * * * * * *
በስሜ ሺ ይነሳሉ
የምትል ቃልህ ቀን ነስታ
እነሆኝ እልፎች አምታቱን
ሰብለ አዳም ግራ ተጋባ።
ለስምህ ታርጋ ለጥፈው
አርገውክ ምርጫ ቅስቀሳ
ለምስልህ ዋጋ ተምነው
ሆንክብን ነፃ ጨረታ።
አቤቱ እርስትህን ባርክ ....
በምርጫው ወይ ተሸንፈን
ወይ አጥተን ሳንገዛህ ብንቀር
ብይንህ ሚዛኑን ስቶ
በፍርድህ ከምንማረር
እዚህ ነኝ የሚል ምልክት
እባክህ ከደጅህ አኑር።
* * * * * * *
ስንፀድቅ ቤታችን ጋብዘን
ስናፅ ከሰማይ ሰቅለን
ስንዘፍን ሶስትዜ አማትበን
ስንገድል እሱ ያቃል ብለን
ስንሰርቅ የግዜር ስጦታ
ስንዘሙት በግዜር ሰላምታ
አንተኑ ባንተው አፍርሰን
ሌላ ግዜር እኛው አብጅተን
ስትመጣ መልክህ ባይለየን
ሗላ ላይ እንዳታዝንብን።
አቤቱ ህዝብህን አድን.....
.... ከክፉም አንተው ጠብቀን
ፅድቅና ኩነኔ መሀል
ያኖርከው ቀጭኑ መስመር ከድፍረት ከእምነት ማጣት
ደብዝዞ ከመደናበር
እንዳሻን እየሰረዝን
እንዳሻን ከምናሰምረው
አቤቱ ፈጣሪያችን ሆይ
ቅፅሩን በግንብ አድርገው።
* * *
አቤቱ ወዴት ቆመሀል
ዝምታህ ከአውራ መብረቅ
ግርማው እጅግ ያስፈራል።
* * *
ዳኒ.B
@getem
@getem
@gebriel_19
"እንቆቅልሽ እማ"
======
እንቆቅልሽ እማ
"ማን ያውቅልህ ልጄ!"
እንቆቅልሽ ስላት "ማን ያውቅልህ" ብላ አይኖቼን የምታይ
በጉየዋ አሙቃ ቀን-አድራጊ ሰናይ
በአይኖቿ አድክማ በጥርሶቿ ገላ
ጥያቄን ልትመልስ እዝነ ህልናዬን አድማሱን ከልላ
እንግዲህ መልሺ
ጸጉሬን እየዳሰስሽ እንባዬን አብሺ
=====
ያለም ጥግጋቱን ቧጭረሽ-መርምረሽ
የእውቀት ስራስሩን ፈርቅቀሽ-ሰራስረሽ
ከጠፋሽ ቅያሱ
ሀገሩን ተይና ዘላለም
ኑሪልኝ እራስሽ ነሽና-የጥያቄው መልሱ
Mezin worku
@getem
@getem
@gwbriel_19
======
እንቆቅልሽ እማ
"ማን ያውቅልህ ልጄ!"
እንቆቅልሽ ስላት "ማን ያውቅልህ" ብላ አይኖቼን የምታይ
በጉየዋ አሙቃ ቀን-አድራጊ ሰናይ
በአይኖቿ አድክማ በጥርሶቿ ገላ
ጥያቄን ልትመልስ እዝነ ህልናዬን አድማሱን ከልላ
እንግዲህ መልሺ
ጸጉሬን እየዳሰስሽ እንባዬን አብሺ
=====
ያለም ጥግጋቱን ቧጭረሽ-መርምረሽ
የእውቀት ስራስሩን ፈርቅቀሽ-ሰራስረሽ
ከጠፋሽ ቅያሱ
ሀገሩን ተይና ዘላለም
ኑሪልኝ እራስሽ ነሽና-የጥያቄው መልሱ
Mezin worku
@getem
@getem
@gwbriel_19
👍1
#የታሰረ ልብ#
በመዳፍህ ጥበብ፥በማዳንህ መክሊት
በመዉደድህ ድርሳን፥በፈገግታህ ዳዊት
ገላየን አሽረህ፥ በለኮስከዉ እሳት
ከዳዊት ጠንክረህ፥ከሰለሞን ልቀህ
ከተራራ ገዝፈህ፥ከሃሳብ ረቀህ
የልቤን ከረጢት፥እንደ ክርታስ ለብሰህ
በስጋ በደሜ፥እንደስኳር ቀልጠህ
ፍቅርን ከወለላዉ፥ከመረቁ ጨልፈህ
ለነገ ሳትሰስት፥ለዛሬ ችረኸኝ
ምነዉ ፥በጥዋት ጠፋህ፥ከጉም ጋር አሰረኸኝ
እንዳልሄድ፥እንዳልቀር፥እንዳልተኛ አርገኸኝ።
ልብ የሌለዉ ደረት፥ታቦት አልባ መቅደስ
የደረቀ ሎሚ፥ ያልተቋጨ ቀሚስ
የነቃ ብርሌ፥ ክር የሌለዉ ፍኑስ
ክንፍ የሌላት ገዴ፥ወላዋይ አረከኝ
በትዝታህ ገመድ፥የኋሊት አስረኸኝ።
ብጠራህ አትሰማኝ፥ብሮጥ አልደርስብህ
ብጠቅስህ አታይ፥ብሸሽህ አልርቅህ
በቆምኩበት ሮጨ፥ባይኔ ስከተልህ
ድንገት ብትሰወር፥ተራራዉ ጋር'ዶህ
ደርበዉ ኩታህን ፥በሩቅ ይጥራኝ ወዝህ
ካይኔ እንኳ ብትጠፋ፥እሽትቼ እንድሸኝህ።
በተኛንበት ሜዳ፥ በመስኩ ላይ፥ ልንከራተት
የቁም ቅዠቴን ልዋዥ፥ሞቴን በሞትህ ላትት
ሳቅህ፥ፋኑስ ይሁነኝ፥ዳናህን ልጥባ በሌሊት
ምስልህን፥አሽዋዉ ላይ፥እወንዙ ዳር ልሳልህ
ልግባ፥ ከፍቅርህ ሙዳይ፥አቤት ልበል በስምህ።
በለስላሳ ጣትህ፥አቅፈህ ባጎረስከኝ
በትዝታህ ሸማ፥ ፈትለህ ባለበስከኝ
ዉሉን ባፍህ ነክሰህ፥ከጉም ጋር አስረኸኝ
ከትናንት አቅርበህ፥ከዛሬ አርቀኸኝ
እንዳልወጣ ፥እንዳልወርድ፥አየር ላይ ሰቀልከኝ።
@getem
@getem
@gebriel_19
በመዳፍህ ጥበብ፥በማዳንህ መክሊት
በመዉደድህ ድርሳን፥በፈገግታህ ዳዊት
ገላየን አሽረህ፥ በለኮስከዉ እሳት
ከዳዊት ጠንክረህ፥ከሰለሞን ልቀህ
ከተራራ ገዝፈህ፥ከሃሳብ ረቀህ
የልቤን ከረጢት፥እንደ ክርታስ ለብሰህ
በስጋ በደሜ፥እንደስኳር ቀልጠህ
ፍቅርን ከወለላዉ፥ከመረቁ ጨልፈህ
ለነገ ሳትሰስት፥ለዛሬ ችረኸኝ
ምነዉ ፥በጥዋት ጠፋህ፥ከጉም ጋር አሰረኸኝ
እንዳልሄድ፥እንዳልቀር፥እንዳልተኛ አርገኸኝ።
ልብ የሌለዉ ደረት፥ታቦት አልባ መቅደስ
የደረቀ ሎሚ፥ ያልተቋጨ ቀሚስ
የነቃ ብርሌ፥ ክር የሌለዉ ፍኑስ
ክንፍ የሌላት ገዴ፥ወላዋይ አረከኝ
በትዝታህ ገመድ፥የኋሊት አስረኸኝ።
ብጠራህ አትሰማኝ፥ብሮጥ አልደርስብህ
ብጠቅስህ አታይ፥ብሸሽህ አልርቅህ
በቆምኩበት ሮጨ፥ባይኔ ስከተልህ
ድንገት ብትሰወር፥ተራራዉ ጋር'ዶህ
ደርበዉ ኩታህን ፥በሩቅ ይጥራኝ ወዝህ
ካይኔ እንኳ ብትጠፋ፥እሽትቼ እንድሸኝህ።
በተኛንበት ሜዳ፥ በመስኩ ላይ፥ ልንከራተት
የቁም ቅዠቴን ልዋዥ፥ሞቴን በሞትህ ላትት
ሳቅህ፥ፋኑስ ይሁነኝ፥ዳናህን ልጥባ በሌሊት
ምስልህን፥አሽዋዉ ላይ፥እወንዙ ዳር ልሳልህ
ልግባ፥ ከፍቅርህ ሙዳይ፥አቤት ልበል በስምህ።
በለስላሳ ጣትህ፥አቅፈህ ባጎረስከኝ
በትዝታህ ሸማ፥ ፈትለህ ባለበስከኝ
ዉሉን ባፍህ ነክሰህ፥ከጉም ጋር አስረኸኝ
ከትናንት አቅርበህ፥ከዛሬ አርቀኸኝ
እንዳልወጣ ፥እንዳልወርድ፥አየር ላይ ሰቀልከኝ።
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
ለአባቴ
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከጥንት ጀምሮ ከወንድ የዘር ግንዱ
ሀያላን ነበሩ ተራራ ’ሚንዱ
ጠቢቦች ነበሩ ጥበብ የሚወዱ
ምን ያደርጋል ታዲያ
አንተን የሚመስሉ መቼ ተወለዱ?
ባልሆን ሙታን ቀስቃሽ
ወደኋላ ገስጋሽ በእውነት ታሪክ ጋሪ
ባልሆን እንኳን ነቢይ ትንቢት ተናጋሪ
በቁንፅሏ እድሜዬ የተገለጠልኝ ያወቅኩት ሀቂቃ
ለራሴ ብነግረው
ምንም ’ማይሰለቸኝ ብደጋግመውም በየሩብ ደቂቃ
አንዳ’ንተ አይነቱ የተመረጠ አባት ህሩየ ህሩያን
ካንተ ኋላ የለ ወደፊት አይመጣ ልክ እንደ ሰለሞን*።
* ጠቢቡ ሰለሞን ከሱ በፊትም ሆነ ከሱ በኋላ እንደሱ ያለ ጠቢብ እንደሌለ፤ እንደማይኖርም፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል @burukassahunC
@getem
@getem
(ቡሩክ ካሳሁን)
ከጥንት ጀምሮ ከወንድ የዘር ግንዱ
ሀያላን ነበሩ ተራራ ’ሚንዱ
ጠቢቦች ነበሩ ጥበብ የሚወዱ
ምን ያደርጋል ታዲያ
አንተን የሚመስሉ መቼ ተወለዱ?
ባልሆን ሙታን ቀስቃሽ
ወደኋላ ገስጋሽ በእውነት ታሪክ ጋሪ
ባልሆን እንኳን ነቢይ ትንቢት ተናጋሪ
በቁንፅሏ እድሜዬ የተገለጠልኝ ያወቅኩት ሀቂቃ
ለራሴ ብነግረው
ምንም ’ማይሰለቸኝ ብደጋግመውም በየሩብ ደቂቃ
አንዳ’ንተ አይነቱ የተመረጠ አባት ህሩየ ህሩያን
ካንተ ኋላ የለ ወደፊት አይመጣ ልክ እንደ ሰለሞን*።
* ጠቢቡ ሰለሞን ከሱ በፊትም ሆነ ከሱ በኋላ እንደሱ ያለ ጠቢብ እንደሌለ፤ እንደማይኖርም፡፡
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል @burukassahunC
@getem
@getem
👍1
🏃♀ሸሸው እንጂ አልራኩም💏
በትዝታህ ገመድ የዋሊት ጠፍረህ
የፊጢኝ አስረኸኝ በግዞትህ አኑረህ
የራኩኝ ቢመስለኝ የሄድኩኝ ካንተ ዘንድ
አሁንም አብሬህ ነኝ በትዝታ መንገድ፡፡
በእምነት ላይ ፀንቶ የቆመው ፍቅራችን
ፅልመትን ለበሰ ተከፍሎ ሀሳባችን፡፡
ውስጤም ተሰበረ ልቤም ያው ወሰነ
መላው እኔነቴ ባንተ ላይ ጨከነ
ከዚያማ ተነሳው ልርቅህ አስቤ
ግና አስመሠልኩኝ ተሸወደ ልቤ
ጥቂት ሸሸው እንጂ መች ራኩኝ ከቀልቤ፡
ዛሬን ነገን መኖር ጭራሽ አቁሜአለው
ኑሬዬ በሙሉ በትዝታ አለም ነው ፤
አኩርፌ ዞር ስል ፈገግታን ችረኸኝ
ከፍቶኝ ያየኸኝ ለት ቀርበህ ምታፅናናኝ
ለዛ ያለው ቀልድህ ተወዳጁ ሳቅህ
ገዳዩ እርምጃህ ሸበላው አቋምህ
አይኖቼን ምታየው በፍቅር አይኖችህ
እጄን ምትዳስሰው በአለንጋ ጣቶችህ
ያ ሸጋው አመልህ ቁም ነገር የበዛው
በፍፁም አልቻልኩም ላፍታ እንኳን ልረሳው ፤
እኔ መቼ ራኩክ አንተን መቼ ተውኩኝ
ብሶብኝ ትዝታህ በፅኑ ታመምኩኝ
ፍቅርህን ፍለጋ በምናብ ባዘንኩኝ
ብዙ ተቅበዘበዝኩ አንተን እያሰብኩኝ፤
ግና ላልመለስ አንዴ ወጥቻለው
የናፍቆቱን እሳት ባልችልም ችላለው
በቃ ወስኛለሁ ላልመለስ ምዬ
ባልርቅም መሸሹ ይሻለኛል ብዬ፡፡
ተፃፈ-በሠላም ሻኪሶ
@getem
@getem
@gebriel_19
በትዝታህ ገመድ የዋሊት ጠፍረህ
የፊጢኝ አስረኸኝ በግዞትህ አኑረህ
የራኩኝ ቢመስለኝ የሄድኩኝ ካንተ ዘንድ
አሁንም አብሬህ ነኝ በትዝታ መንገድ፡፡
በእምነት ላይ ፀንቶ የቆመው ፍቅራችን
ፅልመትን ለበሰ ተከፍሎ ሀሳባችን፡፡
ውስጤም ተሰበረ ልቤም ያው ወሰነ
መላው እኔነቴ ባንተ ላይ ጨከነ
ከዚያማ ተነሳው ልርቅህ አስቤ
ግና አስመሠልኩኝ ተሸወደ ልቤ
ጥቂት ሸሸው እንጂ መች ራኩኝ ከቀልቤ፡
ዛሬን ነገን መኖር ጭራሽ አቁሜአለው
ኑሬዬ በሙሉ በትዝታ አለም ነው ፤
አኩርፌ ዞር ስል ፈገግታን ችረኸኝ
ከፍቶኝ ያየኸኝ ለት ቀርበህ ምታፅናናኝ
ለዛ ያለው ቀልድህ ተወዳጁ ሳቅህ
ገዳዩ እርምጃህ ሸበላው አቋምህ
አይኖቼን ምታየው በፍቅር አይኖችህ
እጄን ምትዳስሰው በአለንጋ ጣቶችህ
ያ ሸጋው አመልህ ቁም ነገር የበዛው
በፍፁም አልቻልኩም ላፍታ እንኳን ልረሳው ፤
እኔ መቼ ራኩክ አንተን መቼ ተውኩኝ
ብሶብኝ ትዝታህ በፅኑ ታመምኩኝ
ፍቅርህን ፍለጋ በምናብ ባዘንኩኝ
ብዙ ተቅበዘበዝኩ አንተን እያሰብኩኝ፤
ግና ላልመለስ አንዴ ወጥቻለው
የናፍቆቱን እሳት ባልችልም ችላለው
በቃ ወስኛለሁ ላልመለስ ምዬ
ባልርቅም መሸሹ ይሻለኛል ብዬ፡፡
ተፃፈ-በሠላም ሻኪሶ
@getem
@getem
@gebriel_19
።።።። ዋ! ።።።።
(በረከት በላይነህ)
አይኔ ወደደሽ ስልሽ፣
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ ስለት
ምኞትሽ ሰመረ
አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው አንደዘበት።
ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ አይን ዛሬም አይሻለው።
ደሞ አንደዚ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሽና።
@lula_al_greeko
@getem
@getem
(በረከት በላይነህ)
አይኔ ወደደሽ ስልሽ፣
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ ስለት
ምኞትሽ ሰመረ
አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው አንደዘበት።
ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ አይን ዛሬም አይሻለው።
ደሞ አንደዚ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሽና።
@lula_al_greeko
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
ከለታት አንድ ቀን
ከማጣህ ከምሞት? ፣ የሚል ምርጫ አቅርባ
የራሷን ጥያቄ ፣ በእንባዋ አጅባ
ብሞት ይሻለኛል ፣ ብላ ነገረችኝ
ስትነግረኝ አመንኳት
እፈትናት ብዬ ፣ እንድትሞት ራኳት ፣ ሳትፈልግ አጣችኝ
።።።
ከእለታት ሁለት ቀን ፣
እሷ ዋሽታ አታውቅም ፣ ለቃሏ ታማኝ ነች
እንዳጣችኝ አውቃ ፣ ይሔኔ ሞታለች
በማለት አስቤ ፣
ለቀብሯ ስዘጋጅ ፣ እሷ ትኖራለች
።።።
ከእለታት ብዙ ቀን ፣
እንዴት አልሞተችም ?
የሚል የእምነት እዳ ፣ መች አብሰለሰለኝ?
አጥታኝ ስትኖር ባያት
እየኖረች መሞት ፣ ምታውቅ መሠለኝ
አምናታለሁና
እሷ አትዋሽምና
@getem
@getem
@gebriel_19
ከለታት አንድ ቀን
ከማጣህ ከምሞት? ፣ የሚል ምርጫ አቅርባ
የራሷን ጥያቄ ፣ በእንባዋ አጅባ
ብሞት ይሻለኛል ፣ ብላ ነገረችኝ
ስትነግረኝ አመንኳት
እፈትናት ብዬ ፣ እንድትሞት ራኳት ፣ ሳትፈልግ አጣችኝ
።።።
ከእለታት ሁለት ቀን ፣
እሷ ዋሽታ አታውቅም ፣ ለቃሏ ታማኝ ነች
እንዳጣችኝ አውቃ ፣ ይሔኔ ሞታለች
በማለት አስቤ ፣
ለቀብሯ ስዘጋጅ ፣ እሷ ትኖራለች
።።።
ከእለታት ብዙ ቀን ፣
እንዴት አልሞተችም ?
የሚል የእምነት እዳ ፣ መች አብሰለሰለኝ?
አጥታኝ ስትኖር ባያት
እየኖረች መሞት ፣ ምታውቅ መሠለኝ
አምናታለሁና
እሷ አትዋሽምና
@getem
@getem
@gebriel_19
👍1
ጨረቃ ሆይ!
((እዮብ ሰብስቤ))
፡
የፍለጋን አቅም
የማግኘትን ጣዕም
የሚያውቅ ይጀግናል፤
የፈራ ግን ልቡ
ጨረቃን ለማየት
ፀሐይ ይለምናል፡፡
እናም ይሁን!
በቀን ተደበቂ በቀን ተሰወሪ
ሲመሽ ግን ይህን አውሪ፡፡
መሻገር ስትፈልግ አዲስ ነገር ማየት
ከለውጥ መጠጋት
ሁሌም ያስፈልጋል ምቾቴ ነው ካልከው
ዓለምህ መዋጋት፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
((እዮብ ሰብስቤ))
፡
የፍለጋን አቅም
የማግኘትን ጣዕም
የሚያውቅ ይጀግናል፤
የፈራ ግን ልቡ
ጨረቃን ለማየት
ፀሐይ ይለምናል፡፡
እናም ይሁን!
በቀን ተደበቂ በቀን ተሰወሪ
ሲመሽ ግን ይህን አውሪ፡፡
መሻገር ስትፈልግ አዲስ ነገር ማየት
ከለውጥ መጠጋት
ሁሌም ያስፈልጋል ምቾቴ ነው ካልከው
ዓለምህ መዋጋት፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19