ግጥም ብቻ 📘
67.6K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
የአብስራ ሳሙኤል

ቀኑስ ከዳኝ እንዳላቅፍሽ 
እንግዲህ ህልሜን ልለመነው 
ወይ ወድጄሽ ላይሞላልኝ 
ያገናኘን ለምንድነው 

— 

ኪዳን አለኝ ከለሊትሽ 
ምስኪን ልቤን ሊያስተሳስር 
በሰመመን ያደርሰኛል 
ከመዳፍሽ ከእግሮችሽ ስር 

— 

ወብ ፈገግታሽ ተስረቅርቆ 
እንደ ንፋስ ሊዳብሰኝ 
ከጽናትሽ ተስፋን ሰርቆ 
ለንጋት ጀንበር ሊያውሰኝ 

— 

ከልካ ይ የለው አጋጅ የለው 
ወይ አይመሩት ወይ አይገሩት 
ተኝቶም ቢሆን ይሄዳል.... 
ልብ እንደው ወዳ 'አፈቀሩት 

— 

አይዞሽ እዛ ትግል የለም 
አረፍ በይ ከታዛው ስር 
ህቡእ ፍቅሬን ታገኛለሽ 
ህልሙን ከአንቺ ሲያስተሳስር 
የእንቅልፉን በር ሲሰረስር።

— 

አይዞሽ እዛ መራዝ የለም 
የተራበ ሁሉ ይጠግባል 
በህይወት የጠወለገው 
አንቺን አይቶ ልቤ ያብባል 
ተስፋ ምኞት ይቀለባል።

— 

**ኪዳን አለኝ ከለሊትሽ 
ምስኪን ልቤን ሊያስተሳስር 
በሰመመን ያደርሰኛል 
ከመዳፍሽ ከእግሮችሽ ስር 

— 

ቀኑስ ከዳኝ እንዳላቅፍሽ
እንግዲ'፣ ህልሜን ልለመነው
ወይ ወድጄሽ ላይሞላልኝ
ያገናኘን ለምንድነው.......


.    .    .    .    .    .    .    .    .    .    .     .   .

@getem
@getem
@getem
31🔥4👍1
ጨዋታዉ ፈረሰ
.
.
ልጅነቴ ልጅነትህን፤
       ለጋነትህ ጮርቃነቴን፤
በትዝታ እየቃኘሁ፤
        ሳቃችንን እየሰማሁ፤
በትዉስታ ምልሰት፤
       በጥሞና ስመለከት።
በድንጋይ ከታትፈን፤
           ማባያ ጨምረን፤
መረቁን ከልሰን፤
          የሰራነዉ ጎመን።
ለሚመጣዉ ዘመን፤
          የእቃቃ ሰርጋችን፤
ሚዜ ስናዘጋጅ ፤
         መኖርን ስንዋጅ፤
ወረቀት ቀዳደን፤
            ቦጭቀን፤ 
ቦጫጭቀን፤
           እየጎዘጎዝን፤
ሰፈር ስናበላሽ፤
       መንደር ስናቆሽሽ፤
ቡና አፍልተን፤
        ቁርሱን በልተን፤
ደግሞ ስንጣላ፤
        ይጠፋናል መላ፤
ኩርኩም ስንቃመስ፤
          ጮኸን ስንዋቀስ፤
መተቃቀፍ በማግስቱ፤
         መንከባለል በክረምቱ፤
ስንቱ አለፈ በጊዜያቱ።
              የእቃቃ ቤታችን፤
ያለምነዉ ኑሯችን፤
          ጨዋታዉ ፈረሰ፤
ዳቦዉ ተቆረሰ።

በዔደን
ታደሰ
@topazionnn

@getem
@getem
51🔥4👍3
የአብስራ ሳሙኤል

እንዲያው እንደ'ድንገት፣ እንዲሁ እንደ'ሁኑ፣
ደርሰን ስንገናኝ አይንሽን ብፈራ፣
"እረስቶኝ ነው" ብለሽ እንዳት'ጨነቂ፣
"ይጠላኛል" ብለሽ እንዳትጠብቂ።

* * *

አይን የማያይው፣ ጆሮ የማይሰማው፤
የልቤን ትርታ አፍኜ በልቤ፣
ወንድነት ቢያንሰኝ ነው፦
አይኔን መሰብሰቤ፣ ፊቴን መሸበቤ...

* * *

እንዲያው እንደ'ድንገት፣
እንዲያው እንደ'ነገው፣
ብዙ አመታት አልፎ፣ ቀን እና ቀን ተጠላልፎ፣
አዲስ ታሪክ ጽፎ፣ አዲስ ህይወት ነድፎ፣
መልክሽ እንደ አደይ፣ እንደ ጤዛ እረግፎ፣
የልጅነት ጊዜ ጭዋታና ፍቅሩን ስናፍቂ...

"ይጠላኛል" ብለሽ፣ "ይረሳኛል" ብለሽ እንዳትጠብቂ!

* * *

የዕድሜ መሰላሉን ብወጣ፣ ብሄድም፣
ህይወትን ብጓዘው፣
አለም ካጣበቡ እልፍ ሴቶች መሀል፦
ያንቺ ሳቅ ብቻ ነው፣ ቀልቤን የሚይዘው።


@getem
@getem
@paappii
31🔥5

[የውሃ ውርደቱ — የዥረት ቅሌቱ......
«መመለሱ ላይቀር ጎብጦ መደፋቱ ፤
"ፋውንቴን ነህ" ተብሎ ወደ ላይ መውጣቱ ።» ]



እኔ ገራም የምንጭ ውሃ .....
ኩልል ያልኩኝ ድምጽ አልባ “ማይ” ፤
ተራራ ላይ የቆምሽውን ክንፋም ውበት
በሩቅ የማይ ።

ክብርስ ለእኔ መውረድ ነው
መፍሰስ ቁልቁል በመሬት ፣
አንቺ ደግሞ ከከፍታው
በክንፍሽ አቅም መቆዬት ።

እንዳይሆን አርጎታል መቼም
ተፈጥሮ ነው እንቆቅልሽ ፤
እንዳንቺ ወደ ደመና
ከፍ ማለት ምን አውቅልሽ?!
ዥረት ነኝ እንዳ
ኗኗሬ
"ውረጅ እንውረድ" ነው
ምልሽ ።



መቼም ኗሪ ዝም አያውቅም ....
ይበልሽ ያሻውን ይፍረድ ፣
ዝቅ በይ “ውረጅ እንውረድ” ።



እንደዚህ ነግሬሽ እንጂ
መሪር ሀቁን አሳውቄ ፤
ውሃ ብሆን (እንዳመሌ)
አልወስድሽም አሳስቄ ።



ውብዬ ...
(ወደድኩም ብዬ.....)
ወዳ
ንቺ ሽቅብ ለመውጣት
ብሞክር እንኳን አልደርስም ፤
ተፈጥሮ ሕጉን አልጥስም ።

አንቺ ግን የመጣሽ እንደሁ.....

«ቤቷ ነበር ያ ደመና ....
ቤቷ ነበር ያ ተራራ ፣
እዩዋት ክንፍ እንደሌላት
በዥረት ጀርባ ተሳፍራ ፣
ወረደች! አይ ተዋረደች
አጃዒብ ፍቅር! » ይባላል

ማ`ናችን ብንቀል ይቀላል?


By @Bekalushumye

@getem
@getem
@getem
26👍3
ጊዜው ተቀይሮ
ፍቅር ጥምቡን ጥሎ
ብናኝ ትቢያ አክሎ
ሁሉ እንኳን ቢሆን ፥ የማይታመን
አንተ ግን እመን
አንተ ግን ታመን
አሁንም በግ ሁን ፥ በፍየል ዘመን ።

ግዴታ አይደለም
ወከባን መልመድ
ወቅትን መዛመድ
ከጊዜው እኩል ፥ አብሮ መራመድ
ስለዚህ ውረድ !

እምቢ በል ገግም
ቀስ ብለህ አዝግም ።
አጉል መሰልጠን አያስፈልግም ።

ክፋት የለውም
በወግ በወጉ
ለገዢ ሀሳብ ቦታ ቢለቁ
ያረጀን ነገር በአዲስ ቢተኩ
ግን ደሞ አሉ - የማይነኩ ።
በጊዜ ፍጥነት የማይለኩ ።

እስካሁን ከመጣው
ገናም ከሚያመጣው
ከቁስ ከማሽኑ
ዘመን የማይሽርህ ፥ አንተ ነህ ፋሽኑ ።

By Hab Hd

@getem
@getem
@paappii
41🔥6😱3🎉1
ዝብርቅርቅ ባለዉ በህይወት አዙሪት፤
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤

ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤

የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤

ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤

ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።

ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤

እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን
ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
23👍4🔥2
#ከተጣሉ_ገፆች_መሃል

የፊቱን እያየ የኋላውን ትቶ
ማንነቱ ጠፍቶት እልህ ጋ ተጋብቶ
          ጎጆውን ቀልሶ
ማን እንደነበረ ረስቶት ጨርሶ
የገዛ እልሁ ደፋው ከፊት ደርሶ።

ብላችሁ ንገሩ
ላገር ለመንደሩ
በምን ጠፋ ቢሉ!

ንሸጣ: ጋሽ ደበበ ሰይፉ (በምን ሞተ ቢሉ)


ዮኒ
     ኣታን   @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍158
እንዴት ነሽ  ስላት
ሳቅ ታበዛለች
ትጫወታለች ፤

< አለሁ ! > 
ትላለች - እንደሞላላት
ቁስሏን የማላውቅ እዬመሰላት ፤

የዐይኗ መደፍረስ
የገጿ ሽክረት
የአንጀቷ ማረር
የልቧ ቁስለት

ጥልቅ ስቃይዋን እዬነገረኝ ፤
እርሷ ግን ሁሌም አንድ የምትለኝ ፤

- - - - - - - - -  አለሁ ደህና ነኝ !

ልዩ ፍጥረት ናት
አይደረሱባትም ፤

ስሟ ሕይወት ነው
ካልተሸከሟት አይረዷትም ፤

በሕመሟ መሳቅ
በቁስሏ ማጌጥ
ታውቅበታለች ፤

ልክ እንደ መሬት
ውኃ'ን ከእሳት ጋር ታቻችላለች ፤

ከራስ ቅራኔ
ከራስ ጋር ሙግት ቢኖርባትም ፤
ከመሳቅ በቀር
በሰው ፊት ማልቀስ አይኾንላትም  ፤

ደህና ነኝ ከሚል
ከአንድ ቃል በቀር ——
  ሌላ አይወጣትም ፤

እወድዳታለሁ ፤

ደህና ነኝ ስትል
ደህና እንዳልሆነች አውቅባታለሁ።

By Tewodros kassa

@getem
@getem
@paappii
74😢12🔥7👍2🤩1
የአብስራ ሳሙኤል

አባ "ደፋር'ሁን" ብለህ እንዳ'ስተማርከኝ፣
እደፍር ብዬ ጦሬን አነሳሁ፤
ግን ሰው ነኝና ለነፍሴ ሳሳሁ።

እናም አባ፣ ያንተንም ምክር ከንቱ ሳላስቀር፣
ጀግና ነኝ ብዬ እንዲው ባክኜ ከሜዳ እንዳልቀር።

     * * *
ከምክርህ ጦሬን፣ ከፍርሀቴ ጋሻን አበጀው፤
እንዲያ ሲሆን ነው ውረድ!

እንውረድ!
ሲሉ የሚበጀው።

ዝናቡ እስኪ'ጠል ሸሸት ማለት፣
ጠለል ማለት መፍራት አይከፋም፣
ውድቀት ነው ብለን ከሳቅንበት ስር፣
መማሪያ የሚሆን ጥበብ አይጠፋም!


by Yabisra Samuel

@getem
@getem
@paappii
43👍4🔥2
እኔ ጭምቱ ሰው
ፍቅር ተለክፌ
ከእድገት ሀገሬ
ለሷ ስል ከንፌ
ሮቤ አለች ሲሉኝ
ሮቤ በርሬ
ሳስስ ስፈልጋት
ስጠይቅ አድሬ
ሸገር ሄደች ሲሉኝ
ባቀና አዲሳባ
እንኳንስ አካሏ
ዳናዋም አልገባ

ባክኜ ባክኜ
ከደከምኩ በኋላ
ምፈልጋት ፍቅሬ
ታየች ከ አሰላ

ገላንን ዱከምን ቢሾፍቱን አልፌ
ከሞጆና ናዝሬት ወንጂ ተገኝቼ
በሶደሬ በኩል ልሂድ ወደ ዴራ
ኢትያን አልፌ እንድገኝ አሰላ።

መነ ጂረኛ ኮ አቲ ቤክተ ላታ
ዮካን ፉዴን ጎንደር ኮ ሊጣ
(ዋ ነን ጀዲ አኒስ አብዲን ሙራ
አፉራ ኬ ዴቤን በርባቸ ኬን ጆራ)

ዮኒ
    ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
24👍8🔥8🤩3
ኪሴ፣ እኔ ፣ እግዜር
(ሳሙኤል አለሙ)

ዝር---ዝር
አምስት ብር
ዝር---ዝር
አስር ብር
ከኪሴ ቁና ፥ ሞልቶ ሲሰፈር
አላውቀውምና ፥ የነገን ነገር
ከንፈሬን እመጣለው።
ስምህን አዋጣለው።
(እግዜር ይስጥልኝ!)

እያለኝ፥ አለ-ማፈሬ
እያለኝ፥ የታጠፈው ብሬ
ባለ-መቀደዱ...
እያለኝ፥ የኪሴ ጨርቁ
ባለ-መተልተሉ...
ግን እንዴት ፥ ያጣ ስንመስል፤
እኔና ኪሴ ፥ አንዲት አንቆስል።

ስለማርያም ሲሉኝ...
ኖሮኝ እጄን እንዳልሰበስበው፤
ስለወላዲቷ ሲሉኝ...
እንዳጣ ሰው
ኪሴን እንዳልደባብሰው፤
ወይ በፀሐዩ
ወይ በዝናቡ
ወይ በንፋሱ
ብቻ ምልክት ስጠኝ ፥ የሚያስታውሱ

@getem
@getem
@getem
👍1710🤩1
" አይ ወጣትነቴ"
             ( ግዮናይ ነኝ)!፧
በባህል ታጥሬ  በ'ምነቴ እየኮራሁ:
ወጣትነቴ አልቆ  እንዳላረጅ ፈራሁ።

በመጠጥ ሰክሬ  ፖሊስ ሳላስቸግር:
ከመንገዱ ቆሜ  ሴቶችን ሳልፎግር።
ለነገ 'ሚበጀኝ  እውቀቱን ሳልቀስም:
ወይ እንደኩዮቼ  ሸጋ ከንፈር ሳልስም።

አወይ ወጣትነት...
በቅኔ ሳልዘምር  ሳልዘፍን ባ'ራራይ:
ወይ አንዷን አቅፌ  አልጋ ሳልከራይ።
ብላክ ሌብል ውስኪን ሳላንቆረቁረው:
የ'ግር አጣጣሌን  ምንም ሳልቀይረው።

ከሜዳ ሳልቦርቅ  ፈረስ እየገራሁ፣
ወጣትነቴ አልቆ  እንዳላረጅ ፈራሁ።

@getem
@getem
@getem
54😢13👎5👍3🤩1
ተስፋ?
.
.
እንደ እምዬ እቅፍ የምንናፍቀዉ፤
ዘወትር ሳንታክት የምንጠብቀዉ፤

ብርሃን እንዲሆን በምናብ የሳልነዉ
በልባችን ያለ ተስፋ ግን ምንድነው?
......................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
40
ፍቅር በዝምታ

ደስ የሚለው ህመም ሰውን የ መውደድ
አዎ ያማል እኮ ለማይገባው ሰው ጨርቅ ጥሎ ማበድ

ባንተ ደስታ መሳቅ የራስን ሀዘን ረስቶ
ደሞ ማዘን መጨነቅ ሀዘንክን አይቶ

ሁሉም ስላንተ ብቻ አንዳች ሳልል ለኔ
ያንተን ህይወት ኖራለው ባክኖ ስለ የኔ

እራሴን ገደልኩት የኔ ምለው አጣው
የኔን ደስታ የኔን ስሜት ከቶ ምን ዋጠው ?

እንዴት ነው የቻልኩት ሁሌ አንተን ማሰቡን
በሁሉም ቦታ ላይ ምስልክን መሳሉን

ለማን ይግባኝ ላቅርብ ላሰማ ስሞታ
ላንተ ብቻ ልቤ ሁሌም እየመታ

ማን ይገባው ይሆን ባወራ የሆዴን
ያልተፈቀደልኝን በጥልቅ መውደዴን

እኔማ መረጥኩኝ ችሎ መቆየቱን
ደና መስሎ መሳቅ መሰንበቱን

ልክ እንደ አምላኬ ልክ እንደ አንዱ ጌታ
ልቤ በ ሰው ፍቅር እየተንገላታ

ለካስ ፍቅር ማለት እግዚአብሔር ማለት ነው
እራሱ ክርስቶስ የተሰቀለው ነው

ታድያ እኔ ማነኝ ወደድኩኝ የምለው
በፍቅር ምክንያት እንዲ የማነባው

ፍቅር ማለት ህመም መሆኑን ባወኩኝ
አንተን በ ማጣቴ እንዲህ ባላዘንኩኝ

መጥቼ እንዳልነግርክ ቤትኛው ድፍረቴ
በህይወቴ ሞልቶ የ ገዛ ጭንቀቴ

እንኳን ግድ ሳይሰጥክ ለኔ ምንም ሳትወደኝ
አድርጎት ፈጣሪ ድንገት እንኳን አንተ እኔን ብትወደኝ

የለኝም አቅሙ ልነግርክ የልቤን ትርታ
ስወድክ ኖራለው ሁሌም በ ዝምታ

ነሀሴ 12

By mhret

@getem
@getem
@paappii
43🔥5👍2
ቢራቢሮ ቢራቢሮ ቢራቢሮ ሆና ነፍሴ፣
መታገሉን አልችልበት ቀን እስኪያልፍ፤
ዝም ነው መልሴ።

እንደ ዛሬ ሆኖ አይቀርም
ነገም ቀኑ ይለወጣል፤
አሁን ትል ነው ያልኩት ገላ፣
ቀን ሲያሽረው ክንፍ ያወጣል።

እቀስማለሁ የአበባን ማር፤
እበራለሁ ከፍ ብዬ።
ጊዜ ደርሶ ያሻረኝን በረከቱን ተቀብዬ፤
ትልነቴን መሬት ጥዬ!

አንተም አንቺም ወገኖቼ፣
ቢራቢሮ ናት ነፍሳችሁ!
ትል እንዳለች አትግደሏት፤
ቀን የማያልፍ ቢመስላችሁ።

ከታገሱት እሺ፣ ካሉት፣
እንደ የ'አቅሙ ሁሉ ይገፋል።
መከራ የህይወት ድልድይ ነው —
የተጽናና ተሻግሮ ያልፋል፤
እምቢ ያለው ይቀጠፋል።


By @YabisraSamuel

@getem
@getem
@getem
28
"ነበር "ይሆናሉ
.
.
ቁርጥራጭ ሃሳቤን፣
ዉስጣዊ ንዳዴን፣
ማንም የማያዉቀዉ ጥልቅ ሰቀቀኔን፣
በነጭ ወረቀት ላይ ሰብስቤ ላሰፍረዉ፣
በቃላቴ ድርድር ጭንቀቴን ላበርደዉ፣

የልቤን ተንፍሼ መዳኔን እያመንኩ፣
ብዕሬን አንስቼ ለመፃፍ ተጣደፍኩ።

ትርጉም አልባ ፊደላትን ቀጣጥዬ፣
በሀዘን ብሶት በመከራ ተከልዬ፣
ወረቀቴ ራሰ በትኩስ እንባዬ።
ለካ..........
የዉስጥን ለመግለጽ ቃላቶች ያጥራሉ፣
ካይን ተሰዉረዉ በነዉ ይጠፋሉ፣
ፍቺ ታጥቶላቸዉ ኢምንት ይሆናሉ።
.............................
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ዘላለም አለሜን ሙሾ አላወርድም፣
ዛሬዬን ለነገ አሳልፌ አልሰጥም።

ፅልመት የዋጣቸዉ አያሌ ቀናቶች፣
እንቅልፍ የራቃቸው ረጃጅም ሌቶች፣

በጊዜ መሪነት ተጥለው ያልፋሉ፣
በአዲስ ተተክተዉ ነበር ይባላሉ፣
ለልጅ ልጅ ሚነገር ታሪክ ይሆናሉ።
......................................................

በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
29👍9
ህልምና አላሚ
(ደሱ ፍቅርኤል)

ትናንት ህልም ነበር
--------ህልም ዛሬም አለ
-----------ነገም ህልም አይጠፋ

አላሚው ብቻ ነው
በወረፋ መጥቶ 'ሚሄድ በወረፋ

በወረፋው መሃል
ዘመን ሸፍጥ ሲያምረው
ጊዜ ተረብ ሲሻ ባ'ገር ላይ ያሾፋል

የሚታለም በዝቶ የሚያልም ይጠፋል።

@getem
@getem
@paappii
31😢3🔥2👍1
አለምን በእፍኝ ልሞላ
        ጊዜን ላቆመው በእግር
ሲሻኝ ከንፌ ልሄድ
        ከአለም ጥበት ግርግር።

አሰኘኝ

ደግሞ
    ዳግም
        ደርሶ
            ፈ
                ገ
                    ግ   
ሳቅ ሳቅ.... በሀሳብ እ
                           ል
                           ም
በሌት ሁሉ አደር
               አንድ ቃል
               አንድ ህልም

አሰብኩሽ
አየሁሽ

ይወረኛል መላ አካሌን ትዝ ባልሽኝ ቁጥር
    ቀጥ....ትር........ቀጥ.....ትር
          በሀሳብ ስመትር።

እኔ አላማረኝም አኳኋኔ ሁሉ ባሳብ ሚሰልለኝ
  አቦ አላውቅልሽም ወደድኩሽ መሰለኝ።


ዮኒ
     ኣታን @yonatoz
43👍15🔥5
ሀገሬን አልሰጥም
---------------------------------

እንቆቅልህ አሉኝ ምኑን አውቅላቸው
መልሱን ከዘነጋሁ ሀገር ልሰጣቸው
በጨዋታ ሰበብ ባገር ስጠኝ ፈሊጥ
ቅኔው አይገባኝም እንዲህ ያለ ሽሙጥ
የሰነፍኩ እንደሁ ስጫወት ብረታ
ከቶ እንዴት ልስጣቸው ሀገር በጨዋታ፡፡?
                     
By @Abuugida
👍6019🔥9
( ተረት ተረት )
============


ያኔ በጥንት ወራት ...
በጣም ሚዋደዱ ጎረቤት ነበሩ
ወይን ይመስል ግተውት በፍቅር የሰከሩ
ቤታቸው አጥር አልባ ሆኖ የሚኖሩ
በድህነት በእርቃን ማይተፉፈሩ
ለሚያያቸው ሁሉ ተስፋን የሚዘሩ
ሁለት ' አንድ ' የሆኑ .. ጎረቤት ነበሩ

ግና ከሰው ስህተት አይጠፋም እንዲሉ
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከአንተ ርቄ ህይወት ከአንተ ርቄ ኑሮ
ለኔ አይከብድ እያሉ
ከቤታቸው መሐል ግድግዳ ተከሉ
ከደጃቸው የእሾህ አጥር አስከለሉ
በለጋ ፍቅራቸው አጉል ቀበጡበት
ተሸነጋገሉ !!

ታዲያ ቀን ሲገፋ ናፍቆት ሲያነዳቸው
የአንዱ ህይወት ያላንዱ አልሞላ ሲላቸው
ዳግም ፍቅር ሲሹ ...
በሞኝነት ተክለው ያቆሙት ግድግዳ
መሠረቱ ጸንቶ አልፈርስም አላቸው
ብቻ በትዝታ ብቻ በወዮታ
በናፍቆት አውራጃ አለፈ ህይወታቸው !

ፍቅሬ ...
እኔና አንቺም ያኔ
እንደኒህ ምስኪናን ጎረቤቶች ነበርን
ብዙ ተጎንጭተን በፍቅር የሰከርን
ከአይን ያውጣቹ እያለ ያየ ሚመርቀን

ግና እንደማይጠፋ ከብረትም ዝገት
ከአንተ ርቄ ኑሮ ካንቺ ርቄ ህይወት
ያላንተ ሳቅ ፌሽታ ያላንቺ መደሰት
አይከብድም እያልን በትኩስ ፍቅራችን
አጉል ቀብጠንበት ..
ክፍተታችን ሰፋ ጉድለታችን በዛ
በእልህ በሞኝነት !!

ታዲያ ጊዜ ደጉ ቀጥቶ ሲያስተምረን
የኔን ጉዞ ያላንቺ .. ያንቺን ጉዞ ያለኔ
ኦናነት ሲነግረን
ምን መልሶ ማፍቀር አንድ መሆን ቢያምረን
ቀብጠን የሄድነውን የየግል ጎዳን
እስክንመለሰው .. አያ ሞት ቀደመን
ትላንት ላይ ብቻ በነበሩ ቀረን !!

By @Kiyorna

@getem
@getem
@paappii
54👍7🔥3😱3