ደመናማ ገጾች.
(የሞገሴ ልጅ)
ምሽት እየጓጉ-
ጭለማን ተግነው - ብርሃንን ሽሽት፣
ብዙዎች ኖረዋል,
መታየት ፈልገው ጠልቷቸው መታየት።
ደመናማ ገጾች-
ተፈርተው መኖሩን - ከክብር ያልቆጠሩ፣
ጭለማን መዋያ፣
መጽናኛ አድርገው - ሲነጋ አደሩ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
(የሞገሴ ልጅ)
ምሽት እየጓጉ-
ጭለማን ተግነው - ብርሃንን ሽሽት፣
ብዙዎች ኖረዋል,
መታየት ፈልገው ጠልቷቸው መታየት።
ደመናማ ገጾች-
ተፈርተው መኖሩን - ከክብር ያልቆጠሩ፣
ጭለማን መዋያ፣
መጽናኛ አድርገው - ሲነጋ አደሩ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
❤17👍8🔥3
(የአብስራ ሳሙኤል)
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
በጆችሽ ዳሰሽ
የራስ ጸጉሬን
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
¶ከንፈር መንከሱ¶
¶ገላ መልበሱ¶
¶ልብስ ተቃደን¶
¶ከጭን ተጋምደን¶
ከላብ ከወዝሽ ጠብታ እስክትቀር
ነይ እንፋቀር
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
¶ዝም ብዬ ልሳም¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
እቅፍ አድርጊያት
ሽሽግ አድርጊያት
ቁስለኛ ነፍሴን
ሀጣን መንፈሴን
በነገርኩሽ ልክ
አልረዳውም እኔም እራሴ
መሸሸጊያ ነው
ገላሽ ለነፍሴ
ሀጢያት ነው ቢሉም
ኩነኔ ቢሉም
የነሱን መጽደቅ ተይው ለነሱ
ገላ ወዝሽ ስላልቀመሱ
ይኮንኑና ይጽደቁ በኛ
........እኛ..........
እኔና አንቺ
ዝም ብለሽ ሳሚኝ አንዳትሰለቺ
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
ተጠምቄበት
ላቦት ወዝሽን
ቃላት እስኪያጥረን በፍቅር ሲቃ
ጨረቃ በሀፍረት በአሽሙር ስቃ
ገላሽን ትፈር
ከውበት እንጂ
አልሰራሽ ከአፈር
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
የራስ ጸጉሬን
እቅፍ አድርገሽ
ሸሽጊኝ ከአሳር
ከህይወት ምሳር
<መዳፍሽ ዳሶኝ>
<ጥርሶችሽ ነክሶኝ>
¶በፍቅር ሲቃ¶
¶ጨረቃ ስቃ¶
ዘ-ፍጥረት አፍሮን
ጭጋግ ሰውሮን
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
<ገላ መልበሱ>
<ከንፈር መንከሱ>
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
@Yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
በጆችሽ ዳሰሽ
የራስ ጸጉሬን
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
¶ከንፈር መንከሱ¶
¶ገላ መልበሱ¶
¶ልብስ ተቃደን¶
¶ከጭን ተጋምደን¶
ከላብ ከወዝሽ ጠብታ እስክትቀር
ነይ እንፋቀር
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
¶ዝም ብዬ ልሳም¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
እቅፍ አድርጊያት
ሽሽግ አድርጊያት
ቁስለኛ ነፍሴን
ሀጣን መንፈሴን
በነገርኩሽ ልክ
አልረዳውም እኔም እራሴ
መሸሸጊያ ነው
ገላሽ ለነፍሴ
ሀጢያት ነው ቢሉም
ኩነኔ ቢሉም
የነሱን መጽደቅ ተይው ለነሱ
ገላ ወዝሽ ስላልቀመሱ
ይኮንኑና ይጽደቁ በኛ
........እኛ..........
እኔና አንቺ
ዝም ብለሽ ሳሚኝ አንዳትሰለቺ
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
ተጠምቄበት
ላቦት ወዝሽን
ቃላት እስኪያጥረን በፍቅር ሲቃ
ጨረቃ በሀፍረት በአሽሙር ስቃ
ገላሽን ትፈር
ከውበት እንጂ
አልሰራሽ ከአፈር
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
የራስ ጸጉሬን
እቅፍ አድርገሽ
ሸሽጊኝ ከአሳር
ከህይወት ምሳር
<መዳፍሽ ዳሶኝ>
<ጥርሶችሽ ነክሶኝ>
¶በፍቅር ሲቃ¶
¶ጨረቃ ስቃ¶
ዘ-ፍጥረት አፍሮን
ጭጋግ ሰውሮን
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
<ገላ መልበሱ>
<ከንፈር መንከሱ>
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
@Yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
👍26❤19👎8🤩2🎉1
ያንድ ቀን ምሽት : ብርድ ቆፈን ሽሽት
ሌቱን ማነጋበት እግዜርን ጠይቄ
የሷን ቤት ጠቆመኝ አደርኩኝ ዘልቄ
ተንኮል እንደነበር ልቤ መች አጣው
ሌቱንም ፍቅሩንም አንግቼለት ወጣሁ።
By @yoseph_gezahegn
@getem
@getem
@paappii
ሌቱን ማነጋበት እግዜርን ጠይቄ
የሷን ቤት ጠቆመኝ አደርኩኝ ዘልቄ
ተንኮል እንደነበር ልቤ መች አጣው
ሌቱንም ፍቅሩንም አንግቼለት ወጣሁ።
By @yoseph_gezahegn
@getem
@getem
@paappii
❤27👍6🤩3🔥1
(የአብስራ ሳሙኤል)
¶እናቷን ብሏት ነው መሰል¶
ጨረቃም ሸ..ሸ..ች ከፍቁሩ
በኩሪፊያ ስትብሰለሰል
ለውበት ተዘጋ በሩ
የከዳ የሸ..ሸ ፍቅርሽ
ታትሞ ከፍጡሩ ሁሉ
አንጋጦ ገጽሽን ሲያይሽ
....... ይላል ይላሉ....
አጣልታው ከ-ዘፍጥረቱ
ጨለማ አደቀደቀ
...... ይላል ጨረቃን
ላንቺ <ቃል> ስላላወቀ
ክፉ <ቃል> አላስለመድሽው
በምን <ቃል> ቁስሉን ይናጋር
.......ይላል ጨረቃን
ለእግዜር ነው የአንቺን ነገር!።
By @Yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
¶እናቷን ብሏት ነው መሰል¶
ጨረቃም ሸ..ሸ..ች ከፍቁሩ
በኩሪፊያ ስትብሰለሰል
ለውበት ተዘጋ በሩ
የከዳ የሸ..ሸ ፍቅርሽ
ታትሞ ከፍጡሩ ሁሉ
አንጋጦ ገጽሽን ሲያይሽ
....... ይላል ይላሉ....
አጣልታው ከ-ዘፍጥረቱ
ጨለማ አደቀደቀ
...... ይላል ጨረቃን
ላንቺ <ቃል> ስላላወቀ
ክፉ <ቃል> አላስለመድሽው
በምን <ቃል> ቁስሉን ይናጋር
.......ይላል ጨረቃን
ለእግዜር ነው የአንቺን ነገር!።
By @Yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
👍21❤16🔥3👎1
ማህሌተ ገንቦ
ባጭር ቀረን ስንል፣ እድሜ ላበደሩን
ቀርፀው ላሳመሩን ለኩሰው ላበሩን
ቺርስ!!
ፊታችንን አይተው እንደተቸገርን፣
ካይናችን ላወቁ
ስለማርያም ብለን እስከንለምናቸው፣
ቆመው ላልጠበቁ
ቺርስ!!
ወድቀው ለማይጥሉ፣ ነግሠው ለሚያነግሡ ነውራችንን አይተው፣ ልከ እንደ ድመት ኩስ ለሚያለባብሱ
ብድር አበድረው፣ ፈጥነው ለሚረሱ
ቺርስ!
ላባ ላረጉልን፣ የመከራ ሸከሙን
ቀልደው ላሳቁን፣ ተጫውተው ላከሙን
በቸከ ዘመን ላይ
ሥጋ ለበስ ትንግርት፣ ሆነው ላስደመሙን
ቺርስ!!!!
By bewuketu seyum
@getem
@getem
@paappii
ባጭር ቀረን ስንል፣ እድሜ ላበደሩን
ቀርፀው ላሳመሩን ለኩሰው ላበሩን
ቺርስ!!
ፊታችንን አይተው እንደተቸገርን፣
ካይናችን ላወቁ
ስለማርያም ብለን እስከንለምናቸው፣
ቆመው ላልጠበቁ
ቺርስ!!
ወድቀው ለማይጥሉ፣ ነግሠው ለሚያነግሡ ነውራችንን አይተው፣ ልከ እንደ ድመት ኩስ ለሚያለባብሱ
ብድር አበድረው፣ ፈጥነው ለሚረሱ
ቺርስ!
ላባ ላረጉልን፣ የመከራ ሸከሙን
ቀልደው ላሳቁን፣ ተጫውተው ላከሙን
በቸከ ዘመን ላይ
ሥጋ ለበስ ትንግርት፣ ሆነው ላስደመሙን
ቺርስ!!!!
By bewuketu seyum
@getem
@getem
@paappii
❤63👍18🔥4🎉3
(የአብስራ ሳሙኤል)
¶ከህይወት ዳርቻ¶
¶የኔና የአንቺ ብቻ¶
<ሆነን>
<ደርሰን>
°°°°ስናይ ተመልሰን
ትዝ አለኝ ትዝ አለሽ
ከትዝታ አይሸሽ
የመጀመሪያው ቀን
ደርሶ ያስተዋወቀን
ከፍጡር ነጥሎ ያውም ከወንድ ዘር
ያርባ ቀን እድሌ ባንቺ ሲመነዘር
መሄጃ ያጣውን እያንከላወሰ
...........ከደጅሽ ደረሰ
የሰናፍጭ ቅንጣት
አንቺን ላለማጣት
የተሳልኩ ይመስል
ውብ የሆነ ምስል
፨ከሙሉ ቀሚስ ጋር ከተሸነሸነ፨
፨የሚያምር ሹሩባ የተጎነጎነ፨
፨ከጉንጮችሽ መሀል፨
፨፨አለች ትንሽ ስርጉድ፨፨
አቤት የእግዚያብሄር ጉድ!!!
ምን ሲል ጋረደበት ?
የወንዱን ልቦና
አልተነካሽ ገና
ያ-ሁሉ ቦዘኔ ደጅሽ ሲርመሰመስ
ሴትነትሽ አይረክስ!።
፨
፨፨፨
ከህይወት ዳርቻ
የኔና አንቺ ብቻ
<አልፈን>
<አሳልፈን>
°°°°ስናይ ተመልሰን
ትዝ አለኝ ትዝ አለሽ
ጀንበር ፀንታ ስትሸሽ
እንዲው ስውተረተር
ሰው የመሆን ነገር
ሞልቶ ለማይሞላ
ሆዴ ስሻ መላ
ጉልበት ሲበዘበዝ
አንቺን አይቶ መፍዘዝ
ምን እድል አመጣሽ
የቱ እምነቴ ቃጣሽ
<ወደምሰራበት>
<ወደምትሰሪበት>
እግዜር ሲያገጣጥም
የዕጣ ፈንታ ግጥም
አንቺን ከኔ ጻፈ
...አንድ ቀን አለፈ...
...ሁለት ቀን አለፈ...
አይንሽን ለመድኩት
መተያየት በዛ
እንዲሁ እንደዋዛ
ተግባባን እንደቀልድ
ተያይዞ መንገድ
...መሸኛኘት በዛ....
....መገባበዝ በዛ....
እንዲሁ እንደዋዛ
¶ወደድኩሽ ወደድሺኝ¶
¶ጠየኩሽ እሺ አልሺኝ¶
በአብርሀም ጋብቻ
የኔና ያንቺ ብቻ
ጭብጨባ ያልበዛበት
ረብሻ ያልበዛበት
ተጸነሰች ህይወት።.....
፨
፨፨፨
ከህይወት ዳርቻ
የኔና አንቺ ብቻ
<ሆነን>
<ደርሰን>
°°°°ስናይ ተመልሰን
መኖርም ያረካል
ውጥኔም ይሳካል
ውል ለሌለው ሀሳብ
ስለሆንሺኝ ርካብ
ዘመን ማሸገሪያ
ባህሩን ማስገሪያ
ከጉንጮችሽ መሀል
፨አለች ትንሽ ስርጉድ፨፨
ሳምኳቸው እንደጉድ ።
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
¶ከህይወት ዳርቻ¶
¶የኔና የአንቺ ብቻ¶
<ሆነን>
<ደርሰን>
°°°°ስናይ ተመልሰን
ትዝ አለኝ ትዝ አለሽ
ከትዝታ አይሸሽ
የመጀመሪያው ቀን
ደርሶ ያስተዋወቀን
ከፍጡር ነጥሎ ያውም ከወንድ ዘር
ያርባ ቀን እድሌ ባንቺ ሲመነዘር
መሄጃ ያጣውን እያንከላወሰ
...........ከደጅሽ ደረሰ
የሰናፍጭ ቅንጣት
አንቺን ላለማጣት
የተሳልኩ ይመስል
ውብ የሆነ ምስል
፨ከሙሉ ቀሚስ ጋር ከተሸነሸነ፨
፨የሚያምር ሹሩባ የተጎነጎነ፨
፨ከጉንጮችሽ መሀል፨
፨፨አለች ትንሽ ስርጉድ፨፨
አቤት የእግዚያብሄር ጉድ!!!
ምን ሲል ጋረደበት ?
የወንዱን ልቦና
አልተነካሽ ገና
ያ-ሁሉ ቦዘኔ ደጅሽ ሲርመሰመስ
ሴትነትሽ አይረክስ!።
፨
፨፨፨
ከህይወት ዳርቻ
የኔና አንቺ ብቻ
<አልፈን>
<አሳልፈን>
°°°°ስናይ ተመልሰን
ትዝ አለኝ ትዝ አለሽ
ጀንበር ፀንታ ስትሸሽ
እንዲው ስውተረተር
ሰው የመሆን ነገር
ሞልቶ ለማይሞላ
ሆዴ ስሻ መላ
ጉልበት ሲበዘበዝ
አንቺን አይቶ መፍዘዝ
ምን እድል አመጣሽ
የቱ እምነቴ ቃጣሽ
<ወደምሰራበት>
<ወደምትሰሪበት>
እግዜር ሲያገጣጥም
የዕጣ ፈንታ ግጥም
አንቺን ከኔ ጻፈ
...አንድ ቀን አለፈ...
...ሁለት ቀን አለፈ...
አይንሽን ለመድኩት
መተያየት በዛ
እንዲሁ እንደዋዛ
ተግባባን እንደቀልድ
ተያይዞ መንገድ
...መሸኛኘት በዛ....
....መገባበዝ በዛ....
እንዲሁ እንደዋዛ
¶ወደድኩሽ ወደድሺኝ¶
¶ጠየኩሽ እሺ አልሺኝ¶
በአብርሀም ጋብቻ
የኔና ያንቺ ብቻ
ጭብጨባ ያልበዛበት
ረብሻ ያልበዛበት
ተጸነሰች ህይወት።.....
፨
፨፨፨
ከህይወት ዳርቻ
የኔና አንቺ ብቻ
<ሆነን>
<ደርሰን>
°°°°ስናይ ተመልሰን
መኖርም ያረካል
ውጥኔም ይሳካል
ውል ለሌለው ሀሳብ
ስለሆንሺኝ ርካብ
ዘመን ማሸገሪያ
ባህሩን ማስገሪያ
ከጉንጮችሽ መሀል
፨አለች ትንሽ ስርጉድ፨፨
ሳምኳቸው እንደጉድ ።
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
❤45👍24🎉3🔥1😱1
🌜🌜🌜🌜
.
.
.....ትዝ ይልሃል ያኔ
እቅፍህ ከተኸኝ ተቀምጠህ ከጎኔ፤
በተመስጦ ሆነን ጨረቃን ስናያት፤
ልባችን ያለዉን በሚስጥር ስንነግራት፤
ትዝ ይልሃል አይደል.......
ላልከዳህ ላትከዳኝ በስሟ ስንምል፤
ዛሬ ቀኑ ከፍቶ ቅናት ይሆን በደል፤
.....አመል አይሉት እድል፤
መሐላችን ጠፍቶ ተጓዝን ለየቅል፤
መገኘት ከፈለክ ከምንወደዉ ስፍራ
.....እጠብቅሃለሁ ከጨረቃ ጋራ።
.............................................
by ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
.....ትዝ ይልሃል ያኔ
እቅፍህ ከተኸኝ ተቀምጠህ ከጎኔ፤
በተመስጦ ሆነን ጨረቃን ስናያት፤
ልባችን ያለዉን በሚስጥር ስንነግራት፤
ትዝ ይልሃል አይደል.......
ላልከዳህ ላትከዳኝ በስሟ ስንምል፤
ዛሬ ቀኑ ከፍቶ ቅናት ይሆን በደል፤
.....አመል አይሉት እድል፤
መሐላችን ጠፍቶ ተጓዝን ለየቅል፤
መገኘት ከፈለክ ከምንወደዉ ስፍራ
.....እጠብቅሃለሁ ከጨረቃ ጋራ።
.............................................
by ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤48👍21🔥5
(የአብስራ ሳሙኤል)
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
እዚህ እታች ሰፈር
ማዳበሪውን እንዳነገተ
ሀይላድ ሲለቅም
መኪና ገጭቶት አንድ ህጻን ሞተ
°°°°°°ይሙት ግድ የለም°°°°
ነበር አልን እንጂ
የኖረው ህይወት ህይወት አይደለም
ትራፊ እንጀራ ለዕልፍ አዕላፍ ያቀራመተ
ባርከው እያለህ
°°°°°°°°°°°ሳትባርክለት እርቦት የሞተ
ቀብሮት ወንድሙን
ከአይኑ አብሶ የእንባ ደሙኑ
።።።።።።ኑሮን ሊጋፋ።።።።።
ለሀይላንድ ልቃሚ አንገት ቢደፋ
"""" """"" """""
ያው እንደወጣ አልተመለሰም
እንደ ጥያቄው እንደ ምኞቱ
የሱን አልን እንጂ
ታሪኩ እራሱ ታሪክ ነው የስንቱ.....
፨፨፨
፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብክን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
[ደሞም አንዲት ሴት]
የቀሚስ ቅዷ የጭኗ ቁስል
የአርብ ዕለት ጌጥክን ግርፋት ምስል
እንደከተበ
አይኖ በምሬት
የራሄል እንባ እያዘነበ
ስታልጎመጉም እንዲ ትል ነበር
የጫንክብኝን የህይወት ቀንበር
<ችዬ ስጋፋው>
ስለምን ወንዱን ስሜት አስከፋው
<የገፋ ባሌን>
ዝሙት ሀጥያቱን ገና ሳለምደው
<ከሞት መራራ>
ብልቱ መርቶ የሚያራምደው
<በእናቱ እንጀራ>
በሰባ እጆቹ ጨፍልቆ ይዞ
የሴት ገላዬን በቁም ገንዞ
¡በድን ሲያስቀረኝ!
ቂም እንዳይመስልህ
በእንባ ዘለላ የሚያናግረኝ
<ይልቅ መዳፍክን>
የአንገት ማህተቤን ወሰድ ከህይወቴ
<አንቆ ሲደፍረኝ>
°°°°°°°°°°°ምስለ ስዕልህ ገዝፎ ከቤቴ
ተስፋ እንዳይሆነኝ
ስንቅ እንዳይሆነኝ
ኖረህ ዝምታ እያስደፈረኝ
ሆድ ይፍጀው እንጂ
ችዬ ያልነገርኩህ ብዙ ነበረኝ።.....
፨፨፨፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
......ደሞም ትዝ አለኝ......
አንዱ ፈላስፋ የተናገረው
ከትቦ ያኖረው
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
ውርቂያኖስ በእንባ እንደመለካት
ተጠማው ያለን በሀሞት ማርካት
<እየቀበሩ>
ማማረር ሀጥያት ብሎ መመካት
<ነድያን አልፎ>
ዲያቆን ፍለጋ መቅድስ ማንኳኳት
.......ደሞም ትዝ አለኝ
ትዝ አለኝ ብዙ........
በሀረግ በስንኝ እንዴት ይቋጠር
ጋን ተሸክሞል ሰው እንደጠጠር
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም ......ዝም
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
የትኛው ጠቢብ ደራሲ ደርሶት ?
የትኛው አምላክ እንባን አብሶት ?
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም..... ዝም
ሰሚ ሳይኖረን አንናዘዝም
፨፨፨፨፨፨
እናም በል እግዜር
መዝገብክን ዝጋው ጆሮ ዳባ አልብስ
የሰማ ሳይሆን
ስሙኝ ያለ ነው የሚያደባብስ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
እዚህ እታች ሰፈር
ማዳበሪውን እንዳነገተ
ሀይላድ ሲለቅም
መኪና ገጭቶት አንድ ህጻን ሞተ
°°°°°°ይሙት ግድ የለም°°°°
ነበር አልን እንጂ
የኖረው ህይወት ህይወት አይደለም
ትራፊ እንጀራ ለዕልፍ አዕላፍ ያቀራመተ
ባርከው እያለህ
°°°°°°°°°°°ሳትባርክለት እርቦት የሞተ
ቀብሮት ወንድሙን
ከአይኑ አብሶ የእንባ ደሙኑ
።።።።።።ኑሮን ሊጋፋ።።።።።
ለሀይላንድ ልቃሚ አንገት ቢደፋ
"""" """"" """""
ያው እንደወጣ አልተመለሰም
እንደ ጥያቄው እንደ ምኞቱ
የሱን አልን እንጂ
ታሪኩ እራሱ ታሪክ ነው የስንቱ.....
፨፨፨
፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብክን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
[ደሞም አንዲት ሴት]
የቀሚስ ቅዷ የጭኗ ቁስል
የአርብ ዕለት ጌጥክን ግርፋት ምስል
እንደከተበ
አይኖ በምሬት
የራሄል እንባ እያዘነበ
ስታልጎመጉም እንዲ ትል ነበር
የጫንክብኝን የህይወት ቀንበር
<ችዬ ስጋፋው>
ስለምን ወንዱን ስሜት አስከፋው
<የገፋ ባሌን>
ዝሙት ሀጥያቱን ገና ሳለምደው
<ከሞት መራራ>
ብልቱ መርቶ የሚያራምደው
<በእናቱ እንጀራ>
በሰባ እጆቹ ጨፍልቆ ይዞ
የሴት ገላዬን በቁም ገንዞ
¡በድን ሲያስቀረኝ!
ቂም እንዳይመስልህ
በእንባ ዘለላ የሚያናግረኝ
<ይልቅ መዳፍክን>
የአንገት ማህተቤን ወሰድ ከህይወቴ
<አንቆ ሲደፍረኝ>
°°°°°°°°°°°ምስለ ስዕልህ ገዝፎ ከቤቴ
ተስፋ እንዳይሆነኝ
ስንቅ እንዳይሆነኝ
ኖረህ ዝምታ እያስደፈረኝ
ሆድ ይፍጀው እንጂ
ችዬ ያልነገርኩህ ብዙ ነበረኝ።.....
፨፨፨፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
......ደሞም ትዝ አለኝ......
አንዱ ፈላስፋ የተናገረው
ከትቦ ያኖረው
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
ውርቂያኖስ በእንባ እንደመለካት
ተጠማው ያለን በሀሞት ማርካት
<እየቀበሩ>
ማማረር ሀጥያት ብሎ መመካት
<ነድያን አልፎ>
ዲያቆን ፍለጋ መቅድስ ማንኳኳት
.......ደሞም ትዝ አለኝ
ትዝ አለኝ ብዙ........
በሀረግ በስንኝ እንዴት ይቋጠር
ጋን ተሸክሞል ሰው እንደጠጠር
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም ......ዝም
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
የትኛው ጠቢብ ደራሲ ደርሶት ?
የትኛው አምላክ እንባን አብሶት ?
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም..... ዝም
ሰሚ ሳይኖረን አንናዘዝም
፨፨፨፨፨፨
እናም በል እግዜር
መዝገብክን ዝጋው ጆሮ ዳባ አልብስ
የሰማ ሳይሆን
ስሙኝ ያለ ነው የሚያደባብስ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
👍36❤16🔥6👎2😁1🎉1
(የአብስራ ሳሙኤል)
አይገርምም ታፈቀርኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
አይገርም
ነጠላ ነፍሶች
በህይወት መንገድ ያልተቆራኙ
አይን ለአይን ሲገናኙ
ምን አሸፈተሽ ምን አሸፈተኝ
የመቅደስ ዕጣን ናርዶስ ሸተተኝ
መግነዜን ፈታሁ ቁስሌ ዳነ
አይገርምም
ግን ይሄ ሁሉ ስለምን ሆነ
.
.
.
.
አይገርም
በጤዛማ ሳር በረሰረሰ
አፌ ከንፈርሽን እንደ ጎረሰ
ጋደም ብለን
ሽቅብ እያየን ሰማይ ሰማይ...ዪን
ጨረቃ አታምርም ብለሽ ስትስቂ
የኮከብ ፍላጭ የአደይ ውዳቂ
የሆነ ገላሽ
ከፊል ተገልቦ አያቃተተኝ
ምን አዘሞተሽ ምን አዘሞተኝ
.
.
.
አይገርም ታፈቀረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
<ፍቅር የሚሉት ጦሶ>
በውደድ ጠልፎ እያቆራኘን
<ጠፈር ያለምነው>
ካፈቀርናት ሴት እቅፍ ተገኘን
"" "" እንኳን ተገኘነን!
ጥበብ ቢበዛ እውቀት በረቅም
የኖረው እንጂ
የፍቅርን ትርጉም ያልኖረው አያቅም ።
.
.
.
አይገርምም ታፈቅረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
አይገርምም ታፈቀርኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
አይገርም
ነጠላ ነፍሶች
በህይወት መንገድ ያልተቆራኙ
አይን ለአይን ሲገናኙ
ምን አሸፈተሽ ምን አሸፈተኝ
የመቅደስ ዕጣን ናርዶስ ሸተተኝ
መግነዜን ፈታሁ ቁስሌ ዳነ
አይገርምም
ግን ይሄ ሁሉ ስለምን ሆነ
.
.
.
.
አይገርም
በጤዛማ ሳር በረሰረሰ
አፌ ከንፈርሽን እንደ ጎረሰ
ጋደም ብለን
ሽቅብ እያየን ሰማይ ሰማይ...ዪን
ጨረቃ አታምርም ብለሽ ስትስቂ
የኮከብ ፍላጭ የአደይ ውዳቂ
የሆነ ገላሽ
ከፊል ተገልቦ አያቃተተኝ
ምን አዘሞተሽ ምን አዘሞተኝ
.
.
.
አይገርም ታፈቀረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
<ፍቅር የሚሉት ጦሶ>
በውደድ ጠልፎ እያቆራኘን
<ጠፈር ያለምነው>
ካፈቀርናት ሴት እቅፍ ተገኘን
"" "" እንኳን ተገኘነን!
ጥበብ ቢበዛ እውቀት በረቅም
የኖረው እንጂ
የፍቅርን ትርጉም ያልኖረው አያቅም ።
.
.
.
አይገርምም ታፈቅረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
👍22❤14🎉1
እንደ እግር ጣት ስር ሙጀሌ
ተሸጉጠው ደሜን ጠጡት
እንደ ወገብ ላይ ቅማል
አካሄዴን ቅጥ አሳጡት
የቋንጃ እከክ ሆነውብኝ
ጥፍሬ ችሎ 'ማይዛቸው
አገባሁ እንጂ አልገደልኩህ
ቆይ ምንድነው ችግራቸው?
አላስራብኩህ ወይ አልጠማህ
ወይ መኝታ አልከለከልኩ
አልባለግሁኝ ፍሬ አልነሳሁ
አላረጥኩኝ ወይ አልመከንኩ...
ጡት አጥብተው ባያስገሱኝ
ከአብራካቸው ባልወለድ
ሚስትህ መሆኔ አይበቃም ወይ
በናትህ ዘንድ ለመወደድ?
አቦ እናትህ አበዙት ኤጭ!
ዘማርቆስ
@wogegnit
@getem
@getem
@getem
ተሸጉጠው ደሜን ጠጡት
እንደ ወገብ ላይ ቅማል
አካሄዴን ቅጥ አሳጡት
የቋንጃ እከክ ሆነውብኝ
ጥፍሬ ችሎ 'ማይዛቸው
አገባሁ እንጂ አልገደልኩህ
ቆይ ምንድነው ችግራቸው?
አላስራብኩህ ወይ አልጠማህ
ወይ መኝታ አልከለከልኩ
አልባለግሁኝ ፍሬ አልነሳሁ
አላረጥኩኝ ወይ አልመከንኩ...
ጡት አጥብተው ባያስገሱኝ
ከአብራካቸው ባልወለድ
ሚስትህ መሆኔ አይበቃም ወይ
በናትህ ዘንድ ለመወደድ?
አቦ እናትህ አበዙት ኤጭ!
ዘማርቆስ
@wogegnit
@getem
@getem
@getem
❤22👍15😁14👎2🔥2🤩1
እንደውም አንገሽግሾኛል
ጓዝሽን ጠቅልለሽ ውጪ
ስንት አመት የከረምሽበት
ልብ ኪራዬን ብቻ አምጪ
የትም ኬትም ኖረሽ
እንደተረፈው ሰው ፍቅር ስትበትኚ
አሁን ኪራዬን ስል
እንዳልኖረበት ሰው ተበዳይ አትሁኚ
ከፋፍዬው እንኳን
ሌላ ምስኪን እንስት እንዳላስገባበት
ልቤ ዳር እስከ ዳር
እንዳትነኩኝ የሚል ፡ ዳናሽ ነበረበት።
አሁን ጥርግ በይ
እንኳን ሌላ ሰው ልብ
እንጦሮጦስ ሂጂ፥
ብቻ ኡኡ ሳልል
ኪራዬን ውለጂ!!
❗️ @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ጓዝሽን ጠቅልለሽ ውጪ
ስንት አመት የከረምሽበት
ልብ ኪራዬን ብቻ አምጪ
የትም ኬትም ኖረሽ
እንደተረፈው ሰው ፍቅር ስትበትኚ
አሁን ኪራዬን ስል
እንዳልኖረበት ሰው ተበዳይ አትሁኚ
ከፋፍዬው እንኳን
ሌላ ምስኪን እንስት እንዳላስገባበት
ልቤ ዳር እስከ ዳር
እንዳትነኩኝ የሚል ፡ ዳናሽ ነበረበት።
አሁን ጥርግ በይ
እንኳን ሌላ ሰው ልብ
እንጦሮጦስ ሂጂ፥
ብቻ ኡኡ ሳልል
ኪራዬን ውለጂ!!
❗️ @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
😁69👍13❤5🔥3🤩3
¹
አላያትም እይልኝ
አልጠብቃት ጠብቅልኝ
ሳሳሁላት ፈራሁላት
አልደረስኩም ድረስላት ።
²
እኔ ከንቱ ሰው.....
የዓለምን እንጂ መውደድ ናፍቆቱን
መቼ ችዬበት የመለኮቱን ?!
ክንፍ የለኝ አልበር ሰይፍ አልሰጠኸኝ
ጎድያለሁ ስል ፍቅር ሞልተኸኝ
ደከምኩኝ አሁን ሆኜ አቅም አልባ
የቀረኝ ጥሪት ጸሎትና እንባ ።
³
ወዳጅ ነኝ ከሚል ሰው....
በድኩም ትከሻ ፍቅር ካነገተ
ትቀርባት የለም ወይ የፈጠርካት አንተ?!
⁴
ከፊቷ ገበታ ሳቋ እንዳይጓደል
ሳር እየመሰላት እንዳትገባ ገደል
(ክንፉን አንጥፎላት እንድትደላደል)
ገብርኤልን ብትልከው
እምቢ አይልህም አይደል?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
አላያትም እይልኝ
አልጠብቃት ጠብቅልኝ
ሳሳሁላት ፈራሁላት
አልደረስኩም ድረስላት ።
²
እኔ ከንቱ ሰው.....
የዓለምን እንጂ መውደድ ናፍቆቱን
መቼ ችዬበት የመለኮቱን ?!
ክንፍ የለኝ አልበር ሰይፍ አልሰጠኸኝ
ጎድያለሁ ስል ፍቅር ሞልተኸኝ
ደከምኩኝ አሁን ሆኜ አቅም አልባ
የቀረኝ ጥሪት ጸሎትና እንባ ።
³
ወዳጅ ነኝ ከሚል ሰው....
በድኩም ትከሻ ፍቅር ካነገተ
ትቀርባት የለም ወይ የፈጠርካት አንተ?!
⁴
ከፊቷ ገበታ ሳቋ እንዳይጓደል
ሳር እየመሰላት እንዳትገባ ገደል
(ክንፉን አንጥፎላት እንድትደላደል)
ገብርኤልን ብትልከው
እምቢ አይልህም አይደል?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
❤71👍17😁4👎1
(የአብስራ ሳሙኤል)
ይሄ የምታይው
የፈረሰ መንገድ ታሪክ እንዳይመስልሽ
እዚህ ጋ'ነው ቃሌ እዚህ ጋ'ነው ቃልሽ
ስጋ የለበሰው
እንደ ሰው እንደ ሰው
ግና......ዛሬ
ስጋሽም በሰበሰ
መንገዱም ፈረሰ
እኔና ትዝታ ብቻ ባለመኖር ውስጥ አለን
ከፈራረሰ ማንነት የህይወትን አጸድ ተክለን!
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
ይሄ የምታይው
የፈረሰ መንገድ ታሪክ እንዳይመስልሽ
እዚህ ጋ'ነው ቃሌ እዚህ ጋ'ነው ቃልሽ
ስጋ የለበሰው
እንደ ሰው እንደ ሰው
ግና......ዛሬ
ስጋሽም በሰበሰ
መንገዱም ፈረሰ
እኔና ትዝታ ብቻ ባለመኖር ውስጥ አለን
ከፈራረሰ ማንነት የህይወትን አጸድ ተክለን!
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
❤16👍8
( ያ ውሻ ... )
===========
ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሀ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ ?
መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
:
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔😔
By @Kiyorna
( ፲፱ - ፮ - ፳፲፮ )
@getem
@getem
@paappii
===========
ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሀ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ ?
መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
:
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔😔
By @Kiyorna
( ፲፱ - ፮ - ፳፲፮ )
@getem
@getem
@paappii
❤61👍23😢6
ማዘን ሲገባኝ ፥ ስትጠፊ ካይኔ
መጻፍ ሲገባኝ ፥ ሙሾ ወይ ቅኔ
(እንጃልኝ እኔ ...)
የጤና አይመስልም ፥ ደህና መሆኔ ።
ትዝ አትዪኝም ወይ ለትንሽ ደቂቃ ?
አትናፍቂኝም ወይ ሳዳምጥ ሙዚቃ ?
ረሳሁሽ በቃ ?
እንጃልኝ
እንጃልኝ
ናፍቆትሽ በኋላ ምን እንዳሰበልኝ ።
ሰው ባይገባው እንጂ አዕምሮው ደንዘዞ
እንዴት 'እፎይ' ይላል ስንት ኮተት ይዞ ?
እባክሽ አታዘግዪብኝ ፥ ስቃዬን ዛሬ ልወጣው
አንቺስ ሄደሻል እሺ
ናፍቆትሽ መች ነው ሚመጣው ?
By Hab HD
@getem
@getem
@paappii
መጻፍ ሲገባኝ ፥ ሙሾ ወይ ቅኔ
(እንጃልኝ እኔ ...)
የጤና አይመስልም ፥ ደህና መሆኔ ።
ትዝ አትዪኝም ወይ ለትንሽ ደቂቃ ?
አትናፍቂኝም ወይ ሳዳምጥ ሙዚቃ ?
ረሳሁሽ በቃ ?
እንጃልኝ
እንጃልኝ
ናፍቆትሽ በኋላ ምን እንዳሰበልኝ ።
ሰው ባይገባው እንጂ አዕምሮው ደንዘዞ
እንዴት 'እፎይ' ይላል ስንት ኮተት ይዞ ?
እባክሽ አታዘግዪብኝ ፥ ስቃዬን ዛሬ ልወጣው
አንቺስ ሄደሻል እሺ
ናፍቆትሽ መች ነው ሚመጣው ?
By Hab HD
@getem
@getem
@paappii
❤38👍17🔥5
(የአብስራ ሳሙኤል)
ስንኝና ቀለም
ከምእናብ አለም
ገጣሚ ሲጽፍሽ
ሰአሊ ሲስልሽ
አርቅቀው
አድንቀው
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
እንዲ ብለው ነበር
ፍክት ያለች ጀምበር
ጨረቃ የምታቅፍ
ዉሀ ላይ የምትጽፍ
ድምጿ የወፍ ዜማ
ጸጉሯ ጥቁር ዞማ
አይኖቿ እንደ ባህር
ሳቋ የሚያሰግር
ከሴትም አንድ ሴት
..
....
የሀሳባቸው ደሴት
ጎዳሽን አልነካም
ማጣትሽን አልተካም
በሀሳባቸው ልክ
በታጠቁት ብዕር
ምኞት ስትሰክር
ያድሉሽ ጀመረ
ውበት ተሳከረ
እውነት ተሳከረ
የለሽም ጨረቃ
ጨለማ ናት ጠልቃ
ፀጉርሽ ተበታትኖ
መልክሽን አደፈ
ይሄ መች ተጻፈ
አልተሳለም ሀቅሽ
የጎደፈ ሳቅሽ
አለቱ ተራራ ቤትሽን የከለለ
ሊያፈርሰው ማን አለ?
ደርሶ ይደበቃል ከምዕናቡ አለም
ሊንደው በስንኝ ሊነቅለው በቀለም
ማን ነበር ከጓዳሽ ?
ማን ነበር የጎዳሽ ?
ሸራ ላይ ስቃሻል
ተጽፈሽ አልቀሻል
ደስታሽ ከአደባባይ
ለገበያ ዋለ
"አሰየው ተባለ"
"ሸጋ ነው ተባለ"
ደርሶ ያየሽ የለ
ባነበቡት ልኬት
ገላሽን ተመኙ
በተረዱሽ መጠን
ደርሰው እየተቀኙ
ያወድሱሽ ጀመር
መፋለስ ሲጀመር
ሀሳብ የወለዳት
አንዲት ስንኩል ፊደል
የሰኣሊው በደል
አምላክ መሆን ቀላል
ሰሪ መሆን ክፉ
ሀዘን ሲጠየፉ
አይዞሽ አላሉሽም
አላስታመሙሽም
ይልቅ በሃሳባቸው
ሸራ ላይ አሳቁሽ
በቃል አደመቁሽ
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
ጨረቃን አቅፈሻል
ሞተሽም ስቀሻል
በድን ቢሆን አንኳ
የሙት መንፈስ መልኳ
ተያቸው በምዕናብ
ካቀፉሽ በሀሳብ
ይፈላሰፉልሽ ቃል እየመረጡ
እንስራሽ ሲሉ ነው ስሪትሽን ያጡ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
ስንኝና ቀለም
ከምእናብ አለም
ገጣሚ ሲጽፍሽ
ሰአሊ ሲስልሽ
አርቅቀው
አድንቀው
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
እንዲ ብለው ነበር
ፍክት ያለች ጀምበር
ጨረቃ የምታቅፍ
ዉሀ ላይ የምትጽፍ
ድምጿ የወፍ ዜማ
ጸጉሯ ጥቁር ዞማ
አይኖቿ እንደ ባህር
ሳቋ የሚያሰግር
ከሴትም አንድ ሴት
..
....
የሀሳባቸው ደሴት
ጎዳሽን አልነካም
ማጣትሽን አልተካም
በሀሳባቸው ልክ
በታጠቁት ብዕር
ምኞት ስትሰክር
ያድሉሽ ጀመረ
ውበት ተሳከረ
እውነት ተሳከረ
የለሽም ጨረቃ
ጨለማ ናት ጠልቃ
ፀጉርሽ ተበታትኖ
መልክሽን አደፈ
ይሄ መች ተጻፈ
አልተሳለም ሀቅሽ
የጎደፈ ሳቅሽ
አለቱ ተራራ ቤትሽን የከለለ
ሊያፈርሰው ማን አለ?
ደርሶ ይደበቃል ከምዕናቡ አለም
ሊንደው በስንኝ ሊነቅለው በቀለም
ማን ነበር ከጓዳሽ ?
ማን ነበር የጎዳሽ ?
ሸራ ላይ ስቃሻል
ተጽፈሽ አልቀሻል
ደስታሽ ከአደባባይ
ለገበያ ዋለ
"አሰየው ተባለ"
"ሸጋ ነው ተባለ"
ደርሶ ያየሽ የለ
ባነበቡት ልኬት
ገላሽን ተመኙ
በተረዱሽ መጠን
ደርሰው እየተቀኙ
ያወድሱሽ ጀመር
መፋለስ ሲጀመር
ሀሳብ የወለዳት
አንዲት ስንኩል ፊደል
የሰኣሊው በደል
አምላክ መሆን ቀላል
ሰሪ መሆን ክፉ
ሀዘን ሲጠየፉ
አይዞሽ አላሉሽም
አላስታመሙሽም
ይልቅ በሃሳባቸው
ሸራ ላይ አሳቁሽ
በቃል አደመቁሽ
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
ጨረቃን አቅፈሻል
ሞተሽም ስቀሻል
በድን ቢሆን አንኳ
የሙት መንፈስ መልኳ
ተያቸው በምዕናብ
ካቀፉሽ በሀሳብ
ይፈላሰፉልሽ ቃል እየመረጡ
እንስራሽ ሲሉ ነው ስሪትሽን ያጡ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
❤42👍21🔥6
ይቅርታ !
ስታቀርቢኝ
ስለራቅኩሽ ፤
ስትወጂኝ
ችላ ስላልኩሽ ፤
ስታንሽልኝ
ስለናቅኩሽ ፤
ኮኮብ
ሰማይ
ፀሐይ
ጨረቃ ... ስታደርጊኝ
እንደ ሰው ስላልቆጠርኩሽ ፤
በነፍስሽ ላይ ስለቀለድኩ
በዕድሜሽ ላይ ስለተጫወትኩ ፤
ውብ ነፍስሽን ስላሳደፍኩ
ስስ ልብሽን ስለሰበርኩ ፤
ልኬ ድረስ ስትመጭ
ልክሽ ድረስ ስላልወረድኩ ፤
ገላሽን
እንደ ትቢያ አፈር
ነፍስሽን
እንደ ዕድፍ ምንጣፍ
ተራ አድርጌ ስለቆጠርኩ ፤
ይቅርታ !
____
አዬሽ
የሰው ስቃዩ ይሄው ነው፤
እኔም ለወደድኳት ያዬሁት መከራ
ያንቺኑ ያኽል ነው ።
By Tewodros kasa
@getem
@getem
@paappii
ስታቀርቢኝ
ስለራቅኩሽ ፤
ስትወጂኝ
ችላ ስላልኩሽ ፤
ስታንሽልኝ
ስለናቅኩሽ ፤
ኮኮብ
ሰማይ
ፀሐይ
ጨረቃ ... ስታደርጊኝ
እንደ ሰው ስላልቆጠርኩሽ ፤
በነፍስሽ ላይ ስለቀለድኩ
በዕድሜሽ ላይ ስለተጫወትኩ ፤
ውብ ነፍስሽን ስላሳደፍኩ
ስስ ልብሽን ስለሰበርኩ ፤
ልኬ ድረስ ስትመጭ
ልክሽ ድረስ ስላልወረድኩ ፤
ገላሽን
እንደ ትቢያ አፈር
ነፍስሽን
እንደ ዕድፍ ምንጣፍ
ተራ አድርጌ ስለቆጠርኩ ፤
ይቅርታ !
____
አዬሽ
የሰው ስቃዩ ይሄው ነው፤
እኔም ለወደድኳት ያዬሁት መከራ
ያንቺኑ ያኽል ነው ።
By Tewodros kasa
@getem
@getem
@paappii
❤65😢31👍21👎13🔥3