ሀቁን ሁሉም ሰው፡
ቢሸፍንም...
ሰው ካለም ክፋት ፡ እንዳይማር
በሴትነት ዘንድ የሚፈፀም
ትልቅ ወንጀል ነው፡
አለማማር!።
እንደ አምላክ በስም ባይመለክ
ባይሰዋለት ዘቢብ ፣ እጣን
ማንም ሸፋፍኖ የማይክደው
ውበት በሰው ላይ
አለው ስልጣን።
መልኳ ያልገነነ ምትደንቅ ሴት
ሀሳቧ አለሙን ቢያገናኝም
በቆንጆ ልጅ ሳቅ ይሸፈናል
ስባሪ ትኩረት ፡ አያገኝም፤
ምንም በህጉ ባይፀድቅ እንኳ
ቃል በቃል ሰፍሮ በትዕማር
ወደው እንዳረጉት የራስ ምርጫ
ትልቅ ወንጀል ነው ፡ አለማማር!።
by @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ቢሸፍንም...
ሰው ካለም ክፋት ፡ እንዳይማር
በሴትነት ዘንድ የሚፈፀም
ትልቅ ወንጀል ነው፡
አለማማር!።
እንደ አምላክ በስም ባይመለክ
ባይሰዋለት ዘቢብ ፣ እጣን
ማንም ሸፋፍኖ የማይክደው
ውበት በሰው ላይ
አለው ስልጣን።
መልኳ ያልገነነ ምትደንቅ ሴት
ሀሳቧ አለሙን ቢያገናኝም
በቆንጆ ልጅ ሳቅ ይሸፈናል
ስባሪ ትኩረት ፡ አያገኝም፤
ምንም በህጉ ባይፀድቅ እንኳ
ቃል በቃል ሰፍሮ በትዕማር
ወደው እንዳረጉት የራስ ምርጫ
ትልቅ ወንጀል ነው ፡ አለማማር!።
by @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
👍23❤18😱6🔥3
ግዴታ ሆኖ — ብለ፟ይሽ
ባላይሽ — ዳግም ደግሜ....
የማይሞላን ባዶ ጊዜ....
(የቀረኝን ግንጥል ዕድሜ....)
በነፍስሽ ጠረን ትዝታ.....
በመንፈስሽ እኖራለሁ ፤
(አልጥልሽም አራግፌ..)
ተሸክሜሽ እዞራለሁ ።
•
ባ`ካሌ — በስሱ ገላ...
በፊቴ — ደግሞ በኋላ....
በጣቴ — ጫፎች አሻራ....
በራሴ — በፀጉሬ ስፍራ ....
(ይዤሽ ነው — ዘመን ምሻገር !)
በልቤ በደሜ — ማገር ፥
በሆንኩት — በቀረኝ ነገር ።
From: Charles Bokouski : “ Living on luck”¹
__
¹ =.......
ⁱᶠ ⁱ ⁿᵉᵛᵉʳ ˢᵉᵉ ʸᵒᵘ ᵃᵍᵃⁱⁿ
ⁱ ʷⁱˡˡ ᵃˡʷᵃʸˢ ᶜᵃʳʳʸ ʸᵒᵘ
ⁱⁿˢⁱᵈᵉ, ᵒᵘᵗ ˢⁱᵈᵉ
ᵒⁿ ᵐʸ ᶠⁱⁿᵍᵉʳ ᵗⁱᵖˢ
ᵃⁿᵈ ᵃᵗ ᵇʳᵃⁱⁿ ᵉᵈᵉᵍᵉˢ
ᵃⁿᵈ ⁱⁿ ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᵒᶠ ʷʰᵃᵗ ⁱ ᵃᵐ ᵒᶠ
ʷʰᵃᵗ ʳᵉᵐᵃⁱⁿˢ
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ባላይሽ — ዳግም ደግሜ....
የማይሞላን ባዶ ጊዜ....
(የቀረኝን ግንጥል ዕድሜ....)
በነፍስሽ ጠረን ትዝታ.....
በመንፈስሽ እኖራለሁ ፤
(አልጥልሽም አራግፌ..)
ተሸክሜሽ እዞራለሁ ።
•
ባ`ካሌ — በስሱ ገላ...
በፊቴ — ደግሞ በኋላ....
በጣቴ — ጫፎች አሻራ....
በራሴ — በፀጉሬ ስፍራ ....
(ይዤሽ ነው — ዘመን ምሻገር !)
በልቤ በደሜ — ማገር ፥
በሆንኩት — በቀረኝ ነገር ።
From: Charles Bokouski : “ Living on luck”¹
__
¹ =.......
ⁱᶠ ⁱ ⁿᵉᵛᵉʳ ˢᵉᵉ ʸᵒᵘ ᵃᵍᵃⁱⁿ
ⁱ ʷⁱˡˡ ᵃˡʷᵃʸˢ ᶜᵃʳʳʸ ʸᵒᵘ
ⁱⁿˢⁱᵈᵉ, ᵒᵘᵗ ˢⁱᵈᵉ
ᵒⁿ ᵐʸ ᶠⁱⁿᵍᵉʳ ᵗⁱᵖˢ
ᵃⁿᵈ ᵃᵗ ᵇʳᵃⁱⁿ ᵉᵈᵉᵍᵉˢ
ᵃⁿᵈ ⁱⁿ ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᵒᶠ ʷʰᵃᵗ ⁱ ᵃᵐ ᵒᶠ
ʷʰᵃᵗ ʳᵉᵐᵃⁱⁿˢ
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
👍36❤25🔥6🤩2😱1
ሰው ነበርኩኝ
ተወለድኩኝ
(ከመሀፀን ወደኩኝ )
አለቀስኩኝ
(ሀዘን ገባኝ ሰው ፈለኩኝ )
አፌን ከፈትኩ
(የሆድ ጥልቀት አወኩ )
በቃኝ አልኩ
( በእድሜ ሰከንኩ )
ጠረን ለየሁ
( ምቾት አየሁ )
ቋንቋ ለመድኩ
(በቆፈሩት ወረድኩ )
መልክ ለየሁ
(እኔን አወኩ አዲስ ካየሁ )
አንተ ግን ለቤቴ
( እንግዳ ላጥንቴ )
ሆነህ የሩቅ ሩቅ
(እንደ ዘመድ እንቅ )
ለምን አደረኩህ ....?
ሴት ነበርኩኝ
የተጣፈ እጣዬ
( ግልጥ ጎባጣዬ )
ሊያውም በእኛ መንደር
( እንቢ ነው መግደርደር )
እያለ ከሚረግጥ
( በዘመን ረመጥ )
በዘር ማን ዘር እሳት
(የምትቃጠል ሴት) !!!
ጨዋ እኮ ነበርኩኝ
አፈነገጥኩልህ
( እራሴን ተውኩልህ )
ወፍ ሆንኩልህ ጫጩት
(ሳይበር እንደ ቀጩት )
ረግጬ ህጌን
(ገላምጬ ወጌን)
ክር እኮ ነበረኝ
የገባሁት ኪዳን
( የመነንኩለት ሀቅ በነፃ ለመዳን )
የወሰዳት ነፍሴን
( ያሳረፈኝ ምናብ ቆርጦ ግሳንግሴን )
ጌታ እኮ ነበረኝ
የልቤ ጉልበቱ
(ሰርክ መስዋእቱ )
የምገብርለት
(ያደረገኝ ዐለት )
ብዙ ነኝ
የማላውቃት እኔ
( ተለየች ከጎኔ )
ወጣች አፈትልካ
( እኔን ላንተ ልካ )
እንደ ሰው ....
(ሞትን እንድቀምሰው)
እንደ ሴት
( እንዳምጥ በምሬት )
እንደ ጨዋ
( እንድፈተን እንድሰዋ )
እንደ አማኝ
(እንድቀበል ሳይቀማኝ )
እንደ ድኩም
( እንዲያነቃኝ ህማም ኩርኩም )
እንደ ብዙ
(አንድ እንድሆን ጠፎ ጓዙ )
ህግ አዝዬ
(ትምክት ልቤን እንዳይንጠኝ )
ተኝቼ እንድነቃ
(አንተን መርጦ ሰጠኝ)
(በእምነት )
@getem
@getem
@getem
ተወለድኩኝ
(ከመሀፀን ወደኩኝ )
አለቀስኩኝ
(ሀዘን ገባኝ ሰው ፈለኩኝ )
አፌን ከፈትኩ
(የሆድ ጥልቀት አወኩ )
በቃኝ አልኩ
( በእድሜ ሰከንኩ )
ጠረን ለየሁ
( ምቾት አየሁ )
ቋንቋ ለመድኩ
(በቆፈሩት ወረድኩ )
መልክ ለየሁ
(እኔን አወኩ አዲስ ካየሁ )
አንተ ግን ለቤቴ
( እንግዳ ላጥንቴ )
ሆነህ የሩቅ ሩቅ
(እንደ ዘመድ እንቅ )
ለምን አደረኩህ ....?
ሴት ነበርኩኝ
የተጣፈ እጣዬ
( ግልጥ ጎባጣዬ )
ሊያውም በእኛ መንደር
( እንቢ ነው መግደርደር )
እያለ ከሚረግጥ
( በዘመን ረመጥ )
በዘር ማን ዘር እሳት
(የምትቃጠል ሴት) !!!
ጨዋ እኮ ነበርኩኝ
አፈነገጥኩልህ
( እራሴን ተውኩልህ )
ወፍ ሆንኩልህ ጫጩት
(ሳይበር እንደ ቀጩት )
ረግጬ ህጌን
(ገላምጬ ወጌን)
ክር እኮ ነበረኝ
የገባሁት ኪዳን
( የመነንኩለት ሀቅ በነፃ ለመዳን )
የወሰዳት ነፍሴን
( ያሳረፈኝ ምናብ ቆርጦ ግሳንግሴን )
ጌታ እኮ ነበረኝ
የልቤ ጉልበቱ
(ሰርክ መስዋእቱ )
የምገብርለት
(ያደረገኝ ዐለት )
ብዙ ነኝ
የማላውቃት እኔ
( ተለየች ከጎኔ )
ወጣች አፈትልካ
( እኔን ላንተ ልካ )
እንደ ሰው ....
(ሞትን እንድቀምሰው)
እንደ ሴት
( እንዳምጥ በምሬት )
እንደ ጨዋ
( እንድፈተን እንድሰዋ )
እንደ አማኝ
(እንድቀበል ሳይቀማኝ )
እንደ ድኩም
( እንዲያነቃኝ ህማም ኩርኩም )
እንደ ብዙ
(አንድ እንድሆን ጠፎ ጓዙ )
ህግ አዝዬ
(ትምክት ልቤን እንዳይንጠኝ )
ተኝቼ እንድነቃ
(አንተን መርጦ ሰጠኝ)
(በእምነት )
@getem
@getem
@getem
❤42👍34🔥5
ይህ ቀዥቃዣ ዝናብ ገላሽን ይንካና
ወዮለት ሰማዩ
ወዮለት ደመና ።
ወፍ አይዘምርልሽ
ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ ።
ደግሞ ይሄን እወቂ
ሆዴ እንደሚበላኝ ካለ እኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ
በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር
በእግዜር ስትመኪ ።
እኔ ነኝ ጠባቂሽ
እኔ ነኝ ደስታሽ
እኔ ነኝ ፈገግታሽ
ሁሉንም የምሆን
እግዜር አላህ ሰማይ
ንፋስ ውሃ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ
ያንቺ ብቻ ታጋይ ።
ክነፍ በዪኝ ልክነፍ
እረፍ በዪኝ ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ በእኔ በኩል ይለፍ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
ወዮለት ሰማዩ
ወዮለት ደመና ።
ወፍ አይዘምርልሽ
ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ ።
ደግሞ ይሄን እወቂ
ሆዴ እንደሚበላኝ ካለ እኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ
በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር
በእግዜር ስትመኪ ።
እኔ ነኝ ጠባቂሽ
እኔ ነኝ ደስታሽ
እኔ ነኝ ፈገግታሽ
ሁሉንም የምሆን
እግዜር አላህ ሰማይ
ንፋስ ውሃ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ
ያንቺ ብቻ ታጋይ ።
ክነፍ በዪኝ ልክነፍ
እረፍ በዪኝ ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ በእኔ በኩል ይለፍ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
❤64👍28👎19🔥9🤩9😁4🎉2
ቁራኛ
ዘመን ያላዳነኝ
ያልፈታኝ ርቀት
ተአምር ያላነጻኝ
ያልፈወሰኝ ጥምቀት
ከናፍቆት ሚነጥል
የታጣልኝ ዳኛ
እድሜ ይፍታህ ያሉት
የፍቅር ምርኮኛ
ሆንኩልሽ ቁራኛ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
ዘመን ያላዳነኝ
ያልፈታኝ ርቀት
ተአምር ያላነጻኝ
ያልፈወሰኝ ጥምቀት
ከናፍቆት ሚነጥል
የታጣልኝ ዳኛ
እድሜ ይፍታህ ያሉት
የፍቅር ምርኮኛ
ሆንኩልሽ ቁራኛ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
❤37👍19😁5👎2🔥2
¯
..ተስማምቶኛል ፀሀይነቷ
መጥፋትን አልሻም ከፊትለፊቷ
ያለርህራሄ ብትወርድም በላዬ
ንዳዷ ጥሞታል ለውርጫም ገላዬ
ልዩ አረገችኝ
ቀየረች ፍጥረቴን ፣
ከጥላ መሸሽ...
ከጥላ መጠለል አድርጋው ህይወቴን።
by @yoseph_Gezahegn
@getem
@getem
@paappii
..ተስማምቶኛል ፀሀይነቷ
መጥፋትን አልሻም ከፊትለፊቷ
ያለርህራሄ ብትወርድም በላዬ
ንዳዷ ጥሞታል ለውርጫም ገላዬ
ልዩ አረገችኝ
ቀየረች ፍጥረቴን ፣
ከጥላ መሸሽ...
ከጥላ መጠለል አድርጋው ህይወቴን።
by @yoseph_Gezahegn
@getem
@getem
@paappii
❤24👍8🤩2🔥1
ሁሉንም ነበረች
አለሌም ጭምትም
እሬትም ወተትም
እሾህም በለስም
በራድም ትኩስም
አሳቢም
ተግባቢም
ሳቂታም ፡ አልቃሻም
አሁን ምንም ነገር
ለመሆን አትሻም።
ኖራለች ከልቧ
ስታልም ስትነካ
ስትጨልም ስትፈካ
ሲቆላት
ሲደላት
ሲከፋት ሲመቻት፥
ለምን እንደሆን እንጃ
ሰው መሆን ሰለቻት!።
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
አለሌም ጭምትም
እሬትም ወተትም
እሾህም በለስም
በራድም ትኩስም
አሳቢም
ተግባቢም
ሳቂታም ፡ አልቃሻም
አሁን ምንም ነገር
ለመሆን አትሻም።
ኖራለች ከልቧ
ስታልም ስትነካ
ስትጨልም ስትፈካ
ሲቆላት
ሲደላት
ሲከፋት ሲመቻት፥
ለምን እንደሆን እንጃ
ሰው መሆን ሰለቻት!።
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
❤42👍25😢17🔥6😱1
(የአብስራ ሳሙኤል)
1....
ተይው
መች ተናግሮ ያቃል
የልቡን
ሀሳቡን
ወንድ አይደለ
እያነባ ይስቃል
ደና ነኝ እያለ
አለ
መኖር ካሉት
በእግዜር ምስጋና ቢኩሉት
በፈገግታ ቢቀበር እንባ
ወንድ አይደለ
ይመስገነው ብሎ ገባ
በትጨልምም
በትዘምም
ዙፋኑ ናት
ጎጆው ..... ማጀቱ
ቤቱ
የጻፈበት ገድል
የኑሮ ድል
የወዝ ዋጋ የላብ ፍሬ
ደና ነኝ ለዛሬ
2....
ተይው
ወንድ አይደለ
መች ደህና ሆኖ ያቃል
ደህና ነኝ እያለ
በገረባው
በሲጃራው
በእጣን ጢሱ
የተረሱ
መአት ብሶት
የጭስ ለቅሶ
አይን ያሟሿል
ሌላን ደርሶ
ሆድ አስብሶ
ግን ግድ ነው
ዛሬ የዱአ ከተገኘ
ይመስገን ነው
ደህና ነን ነው
3....
ተይው
ወንድ አይደለ
ባሬላ ጭኖ
ኩንታል ተጭኖ
መሪ ጨብጦ
ከብቶች እረግጦ
ባመጣት ሀሴት
ላፈቀራት ሴት
የ አበባ ጉንጉን
የወግ የወጉን
የወርቅ ሀብል
የባዕድ መብል
በርገር
ቢዛ
ማክያቶ
ተገባብዞ
ተጎንጭቶ
ሩም ይዞ
ባናት ባናት መዳራት
ፍቅር መስራት
ከሰመረ ገላዋን
ካልሆነም ጸጸት ታቅፎ
ትዝታ በውሀ አራግፎ
ደህና ነኝ ነው
ወንድ አይደለ
የልቡን ጠባሳ የሚያወራ ማን ነው
4....
ተይው
አትጠይቂው
እንዴት ዋልክ እያልሽ ?
ላትጸድቂ በነፍሱ
ደህና ባይሆን እንኳ
ደህና ነኝ ብቻ ነው
የወንድ ልጅ መልሱ!
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
1....
ተይው
መች ተናግሮ ያቃል
የልቡን
ሀሳቡን
ወንድ አይደለ
እያነባ ይስቃል
ደና ነኝ እያለ
አለ
መኖር ካሉት
በእግዜር ምስጋና ቢኩሉት
በፈገግታ ቢቀበር እንባ
ወንድ አይደለ
ይመስገነው ብሎ ገባ
በትጨልምም
በትዘምም
ዙፋኑ ናት
ጎጆው ..... ማጀቱ
ቤቱ
የጻፈበት ገድል
የኑሮ ድል
የወዝ ዋጋ የላብ ፍሬ
ደና ነኝ ለዛሬ
2....
ተይው
ወንድ አይደለ
መች ደህና ሆኖ ያቃል
ደህና ነኝ እያለ
በገረባው
በሲጃራው
በእጣን ጢሱ
የተረሱ
መአት ብሶት
የጭስ ለቅሶ
አይን ያሟሿል
ሌላን ደርሶ
ሆድ አስብሶ
ግን ግድ ነው
ዛሬ የዱአ ከተገኘ
ይመስገን ነው
ደህና ነን ነው
3....
ተይው
ወንድ አይደለ
ባሬላ ጭኖ
ኩንታል ተጭኖ
መሪ ጨብጦ
ከብቶች እረግጦ
ባመጣት ሀሴት
ላፈቀራት ሴት
የ አበባ ጉንጉን
የወግ የወጉን
የወርቅ ሀብል
የባዕድ መብል
በርገር
ቢዛ
ማክያቶ
ተገባብዞ
ተጎንጭቶ
ሩም ይዞ
ባናት ባናት መዳራት
ፍቅር መስራት
ከሰመረ ገላዋን
ካልሆነም ጸጸት ታቅፎ
ትዝታ በውሀ አራግፎ
ደህና ነኝ ነው
ወንድ አይደለ
የልቡን ጠባሳ የሚያወራ ማን ነው
4....
ተይው
አትጠይቂው
እንዴት ዋልክ እያልሽ ?
ላትጸድቂ በነፍሱ
ደህና ባይሆን እንኳ
ደህና ነኝ ብቻ ነው
የወንድ ልጅ መልሱ!
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
❤41👍20🔥7
ደመናማ ገጾች.
(የሞገሴ ልጅ)
ምሽት እየጓጉ-
ጭለማን ተግነው - ብርሃንን ሽሽት፣
ብዙዎች ኖረዋል,
መታየት ፈልገው ጠልቷቸው መታየት።
ደመናማ ገጾች-
ተፈርተው መኖሩን - ከክብር ያልቆጠሩ፣
ጭለማን መዋያ፣
መጽናኛ አድርገው - ሲነጋ አደሩ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
(የሞገሴ ልጅ)
ምሽት እየጓጉ-
ጭለማን ተግነው - ብርሃንን ሽሽት፣
ብዙዎች ኖረዋል,
መታየት ፈልገው ጠልቷቸው መታየት።
ደመናማ ገጾች-
ተፈርተው መኖሩን - ከክብር ያልቆጠሩ፣
ጭለማን መዋያ፣
መጽናኛ አድርገው - ሲነጋ አደሩ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
❤17👍8🔥3
(የአብስራ ሳሙኤል)
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
በጆችሽ ዳሰሽ
የራስ ጸጉሬን
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
¶ከንፈር መንከሱ¶
¶ገላ መልበሱ¶
¶ልብስ ተቃደን¶
¶ከጭን ተጋምደን¶
ከላብ ከወዝሽ ጠብታ እስክትቀር
ነይ እንፋቀር
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
¶ዝም ብዬ ልሳም¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
እቅፍ አድርጊያት
ሽሽግ አድርጊያት
ቁስለኛ ነፍሴን
ሀጣን መንፈሴን
በነገርኩሽ ልክ
አልረዳውም እኔም እራሴ
መሸሸጊያ ነው
ገላሽ ለነፍሴ
ሀጢያት ነው ቢሉም
ኩነኔ ቢሉም
የነሱን መጽደቅ ተይው ለነሱ
ገላ ወዝሽ ስላልቀመሱ
ይኮንኑና ይጽደቁ በኛ
........እኛ..........
እኔና አንቺ
ዝም ብለሽ ሳሚኝ አንዳትሰለቺ
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
ተጠምቄበት
ላቦት ወዝሽን
ቃላት እስኪያጥረን በፍቅር ሲቃ
ጨረቃ በሀፍረት በአሽሙር ስቃ
ገላሽን ትፈር
ከውበት እንጂ
አልሰራሽ ከአፈር
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
የራስ ጸጉሬን
እቅፍ አድርገሽ
ሸሽጊኝ ከአሳር
ከህይወት ምሳር
<መዳፍሽ ዳሶኝ>
<ጥርሶችሽ ነክሶኝ>
¶በፍቅር ሲቃ¶
¶ጨረቃ ስቃ¶
ዘ-ፍጥረት አፍሮን
ጭጋግ ሰውሮን
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
<ገላ መልበሱ>
<ከንፈር መንከሱ>
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
@Yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
በጆችሽ ዳሰሽ
የራስ ጸጉሬን
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
¶ከንፈር መንከሱ¶
¶ገላ መልበሱ¶
¶ልብስ ተቃደን¶
¶ከጭን ተጋምደን¶
ከላብ ከወዝሽ ጠብታ እስክትቀር
ነይ እንፋቀር
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
¶ዝም ብዬ ልሳም¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
እቅፍ አድርጊያት
ሽሽግ አድርጊያት
ቁስለኛ ነፍሴን
ሀጣን መንፈሴን
በነገርኩሽ ልክ
አልረዳውም እኔም እራሴ
መሸሸጊያ ነው
ገላሽ ለነፍሴ
ሀጢያት ነው ቢሉም
ኩነኔ ቢሉም
የነሱን መጽደቅ ተይው ለነሱ
ገላ ወዝሽ ስላልቀመሱ
ይኮንኑና ይጽደቁ በኛ
........እኛ..........
እኔና አንቺ
ዝም ብለሽ ሳሚኝ አንዳትሰለቺ
፨ከንፈር ከንፈሬን፨
፨ከንፈር ከንፈርሽን፨
ተጠምቄበት
ላቦት ወዝሽን
ቃላት እስኪያጥረን በፍቅር ሲቃ
ጨረቃ በሀፍረት በአሽሙር ስቃ
ገላሽን ትፈር
ከውበት እንጂ
አልሰራሽ ከአፈር
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
፨ከንፈር፨
፨ከንፈሬን፨
የራስ ጸጉሬን
እቅፍ አድርገሽ
ሸሽጊኝ ከአሳር
ከህይወት ምሳር
<መዳፍሽ ዳሶኝ>
<ጥርሶችሽ ነክሶኝ>
¶በፍቅር ሲቃ¶
¶ጨረቃ ስቃ¶
ዘ-ፍጥረት አፍሮን
ጭጋግ ሰውሮን
ጽድቅ እስኪመስል
ፈውስ እስኪመስል
<ገላ መልበሱ>
<ከንፈር መንከሱ>
¶ዝም ብለሽ ስሚኝ¶
¶ዝም ብለሽ ሳሚኝ¶
@Yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
👍26❤19👎8🤩2🎉1
ያንድ ቀን ምሽት : ብርድ ቆፈን ሽሽት
ሌቱን ማነጋበት እግዜርን ጠይቄ
የሷን ቤት ጠቆመኝ አደርኩኝ ዘልቄ
ተንኮል እንደነበር ልቤ መች አጣው
ሌቱንም ፍቅሩንም አንግቼለት ወጣሁ።
By @yoseph_gezahegn
@getem
@getem
@paappii
ሌቱን ማነጋበት እግዜርን ጠይቄ
የሷን ቤት ጠቆመኝ አደርኩኝ ዘልቄ
ተንኮል እንደነበር ልቤ መች አጣው
ሌቱንም ፍቅሩንም አንግቼለት ወጣሁ።
By @yoseph_gezahegn
@getem
@getem
@paappii
❤27👍6🤩3🔥1