................
ዛሬም እንደትናትና
ናፈቅሺኝ ከንደገና
ተገዝ የበዛበት የቀናው ጎዳና
ውብ መልክሽን ሳለ
ከመንገዱ መሀል ላመል የበቀለው
ዘንባባና ጥዱ ሳቅሽን የመሰለው
ፈገግታሽን ኳለ!
የለማኝ የተሽከርካሪው የማቲው
ጫጫታ እራቀኝ
ከመንገድ መሀል ገትሮ
በህላዌ አመጠቀኝ
አካልሽ ከኔ ባያርፍም፤ጥላሽን ዳብሼ ጸናሁ
ዳናሽ ከከተበበት፤በጽናት ልቤን መራሁ
ደረስኩብሽ ስል ስትርቂኝ
ቀሚሽን ያዝኩ ስል ስትነጥቂኝ
ማፍቀር ሲያደናቅፈኝ
ተስፈ ሆኖኝ እንቅፋት
በበቀል እንዲሽርልኝ
የነፍሴን ስብር እጥፈት
ትናንት እንዳልነበረ
መዳፍሽ እንዳልዳበሰው
አላውቅም በሚል ቃል ክጄ
ፍቅርሽን እንዳላረክሰው
ትዝታሽ መግል ሆነብኝ ናፍቆትሽ የጊዜ ቁስል
ጎዳናው ይፈካልኛል ጫጫታው መልክሽን ሲስል
መከተል
መሄድ
መጓዝ ነው
ጥላዋን ያፈቀረ ሰው
መንገዱ የቀናለትን ልመና እንዳይመልሰው
ቃላት አይከጅሉትም ገላ ያልበቃውን ሰው
ጠልቼሽ እንደዲድንልኝ
የፍቅርሽ የነፍሴ ቁስል
ሸሽቼሽ እንዲሰምርልኝ
ህይወቴ ህልም እንዲመስል
ሀሞቴን አምርሬ
ሀጥያትሽን ደርድሬ
እረሳሁሽ ብዬ መንፈሴን ሳጽናና
ትናፍቂኝ ጀመር ዛሬም እንደገና
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ዛሬም እንደትናትና
ናፈቅሺኝ ከንደገና
ተገዝ የበዛበት የቀናው ጎዳና
ውብ መልክሽን ሳለ
ከመንገዱ መሀል ላመል የበቀለው
ዘንባባና ጥዱ ሳቅሽን የመሰለው
ፈገግታሽን ኳለ!
የለማኝ የተሽከርካሪው የማቲው
ጫጫታ እራቀኝ
ከመንገድ መሀል ገትሮ
በህላዌ አመጠቀኝ
አካልሽ ከኔ ባያርፍም፤ጥላሽን ዳብሼ ጸናሁ
ዳናሽ ከከተበበት፤በጽናት ልቤን መራሁ
ደረስኩብሽ ስል ስትርቂኝ
ቀሚሽን ያዝኩ ስል ስትነጥቂኝ
ማፍቀር ሲያደናቅፈኝ
ተስፈ ሆኖኝ እንቅፋት
በበቀል እንዲሽርልኝ
የነፍሴን ስብር እጥፈት
ትናንት እንዳልነበረ
መዳፍሽ እንዳልዳበሰው
አላውቅም በሚል ቃል ክጄ
ፍቅርሽን እንዳላረክሰው
ትዝታሽ መግል ሆነብኝ ናፍቆትሽ የጊዜ ቁስል
ጎዳናው ይፈካልኛል ጫጫታው መልክሽን ሲስል
መከተል
መሄድ
መጓዝ ነው
ጥላዋን ያፈቀረ ሰው
መንገዱ የቀናለትን ልመና እንዳይመልሰው
ቃላት አይከጅሉትም ገላ ያልበቃውን ሰው
ጠልቼሽ እንደዲድንልኝ
የፍቅርሽ የነፍሴ ቁስል
ሸሽቼሽ እንዲሰምርልኝ
ህይወቴ ህልም እንዲመስል
ሀሞቴን አምርሬ
ሀጥያትሽን ደርድሬ
እረሳሁሽ ብዬ መንፈሴን ሳጽናና
ትናፍቂኝ ጀመር ዛሬም እንደገና
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍30❤21🔥2😢1
ቤት እማ ጨዋ ነሽ፣
እንኳን ሌላ ሌላ እኔንም አታይም፣
ግን እድሜ ለሱሱ፣
ወተሽ ወዳጅ ካየሽ አታልፊም አትተይም።
የሸመገለን ወንድ፣
በሰለቸ ዐይንሽ ዕያየሽ ወጠምሻ፣
የሱን መድሃኒት፣
አርገሽ ለቀን ያዝሽው የኔን ማስታገሻ
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
እንኳን ሌላ ሌላ እኔንም አታይም፣
ግን እድሜ ለሱሱ፣
ወተሽ ወዳጅ ካየሽ አታልፊም አትተይም።
የሸመገለን ወንድ፣
በሰለቸ ዐይንሽ ዕያየሽ ወጠምሻ፣
የሱን መድሃኒት፣
አርገሽ ለቀን ያዝሽው የኔን ማስታገሻ
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
👍20❤6😁1
..........
ላመልክህ አልኩና
ስምክን እየጠራሁ፤በእንባ ላመሰግን
ይታየኛል ደሞ
ጸሎቴ በሙሉ፤ደሮሶ ጉም ሲዘግን
እኔ አንተን አይደለው
በመከራ መጽናት፤ከቶ አላውቅበትም
ለሚገርፈኝ ሁሉ
ይቅር በለው እያልኩ፤አልጸልይለትም
ላመልክህ እልና
ምስጋናዬን ትቸው እየኝ ስብሰለሰል
ሁለት ስለት መሆን ይቃጣኛል መሰል
በስምህ መጽውቶ
ስምህን ተጣርቶ እራፊ ለሚያጣ
አንበጣ ብትልክ መአት ብታመጣ
ይህ አይደል ተአምር
ይህ አይደል አምልኮት
እሳት ላዘነበ
ውሀ ነኝ መለኮት
ታድን እነደሆነ
እሲቲ አሁን አድነኝ፤ቀናት አይቀጠር
ጋንን ለደገፈ፤ይከብደዋል ጠጠር
.....
......
ላመልክህ እልና
....
......
ደሞ እተወዋለው
መካድ እንዳይመስል
ክህደቴም ሀቅ አለው
...
.....
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ላመልክህ አልኩና
ስምክን እየጠራሁ፤በእንባ ላመሰግን
ይታየኛል ደሞ
ጸሎቴ በሙሉ፤ደሮሶ ጉም ሲዘግን
እኔ አንተን አይደለው
በመከራ መጽናት፤ከቶ አላውቅበትም
ለሚገርፈኝ ሁሉ
ይቅር በለው እያልኩ፤አልጸልይለትም
ላመልክህ እልና
ምስጋናዬን ትቸው እየኝ ስብሰለሰል
ሁለት ስለት መሆን ይቃጣኛል መሰል
በስምህ መጽውቶ
ስምህን ተጣርቶ እራፊ ለሚያጣ
አንበጣ ብትልክ መአት ብታመጣ
ይህ አይደል ተአምር
ይህ አይደል አምልኮት
እሳት ላዘነበ
ውሀ ነኝ መለኮት
ታድን እነደሆነ
እሲቲ አሁን አድነኝ፤ቀናት አይቀጠር
ጋንን ለደገፈ፤ይከብደዋል ጠጠር
.....
......
ላመልክህ እልና
....
......
ደሞ እተወዋለው
መካድ እንዳይመስል
ክህደቴም ሀቅ አለው
...
.....
By @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍51❤11👎7😱6😢6🔥3🤩1
..........
አፍቃሪሽ በሙሉ
ቅኔ ሲቀኝልሽ
ዜማ ሲያወርድልሽ
እኔም በተራዬ
ሰምተሽ የማታቂው
ምን ልዘምርልሽ
አይተሽ ያልገፋሽው
ምን ልገብርልሽ
እጅ መንሻ እንዲሆን
እጣንና ከርቤ
ወይ ሽቶ ና ሰንደል
መሰዋት አቅርቤ
ባንቺው መጀን ልበል
በፈጠረኝ አምላክ
ለፈጠራት ሴት ስል
በስምሽ ልታበል
ካልበቃት ዝማሬ
ኩሩ ልቧን ማርኮት
ነፍሴን ገበርኩላት
ፍቅር ሆኖኝ አምልኮት
አፍቃሪሽ በሙሉ
ባንቺው መጀን ሲሉ
ካንቺ የሚደበቅ የለም አንዲት ነገር
ባልሰማሽው ቋንቋ ማፍቀሬን ልናገር
ከዘለላ ጸጉርሽ
በመላ ቆንጥሬ
ባንቺው መጀን እያልኩ
መጥቻለሁ ፍቅሬ
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
አፍቃሪሽ በሙሉ
ቅኔ ሲቀኝልሽ
ዜማ ሲያወርድልሽ
እኔም በተራዬ
ሰምተሽ የማታቂው
ምን ልዘምርልሽ
አይተሽ ያልገፋሽው
ምን ልገብርልሽ
እጅ መንሻ እንዲሆን
እጣንና ከርቤ
ወይ ሽቶ ና ሰንደል
መሰዋት አቅርቤ
ባንቺው መጀን ልበል
በፈጠረኝ አምላክ
ለፈጠራት ሴት ስል
በስምሽ ልታበል
ካልበቃት ዝማሬ
ኩሩ ልቧን ማርኮት
ነፍሴን ገበርኩላት
ፍቅር ሆኖኝ አምልኮት
አፍቃሪሽ በሙሉ
ባንቺው መጀን ሲሉ
ካንቺ የሚደበቅ የለም አንዲት ነገር
ባልሰማሽው ቋንቋ ማፍቀሬን ልናገር
ከዘለላ ጸጉርሽ
በመላ ቆንጥሬ
ባንቺው መጀን እያልኩ
መጥቻለሁ ፍቅሬ
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
❤43👍31🔥8😁8
የልጅነት ፍቅር እንደምን ያሰኛል
መቼም አልተዉህም ሀሳብ አይግባህ
እንጠለጠል ነበር ብችል ከጀርባህ
ስህተት አልነበረም እኔን መምረጥህ
በምክንያት ነው የገባሁት ከልብህ
አልቀየምህም ብትጠነቀቅ
ማየት ግን አልችልም ስትጨናነቅ
እንደምፈልግህ እባክህ እወቅ
ውስጥህን አድምጠው እኔን ሲናፍቅ
ትንሽ አደግ ሲሉስ?
ያኔ ልቤ አንተን እየመረመረ
አሁን እንደሆንከው ይፈራ ነበረ
ፍቅር አመሉ ነው ባደረበት አካል
መሸነፍ ሊያስተምር ጦርነት ይፈጥራል
By Mahlet
@getem
@getem
@getem
መቼም አልተዉህም ሀሳብ አይግባህ
እንጠለጠል ነበር ብችል ከጀርባህ
ስህተት አልነበረም እኔን መምረጥህ
በምክንያት ነው የገባሁት ከልብህ
አልቀየምህም ብትጠነቀቅ
ማየት ግን አልችልም ስትጨናነቅ
እንደምፈልግህ እባክህ እወቅ
ውስጥህን አድምጠው እኔን ሲናፍቅ
ትንሽ አደግ ሲሉስ?
ያኔ ልቤ አንተን እየመረመረ
አሁን እንደሆንከው ይፈራ ነበረ
ፍቅር አመሉ ነው ባደረበት አካል
መሸነፍ ሊያስተምር ጦርነት ይፈጥራል
By Mahlet
@getem
@getem
@getem
👍31❤10👎2
ቤት እማ ጨዋ ነሽ፣
እንኳን ሌላ ሌላ እኔንም አታይም፣
ግን እድሜ ለሱሱ፣
ወተሽ ወዳጅ ካየሽ አታልፊም አትተይም።
የሸመገለን ወንድ፣
በሰለቸ ዐይንሽ ዕያየሽ ወጠምሻ፣
የሱን መድሃኒት፣
አርገሽ ለቀን ያዝሽው የኔን ማስታገሻ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
እንኳን ሌላ ሌላ እኔንም አታይም፣
ግን እድሜ ለሱሱ፣
ወተሽ ወዳጅ ካየሽ አታልፊም አትተይም።
የሸመገለን ወንድ፣
በሰለቸ ዐይንሽ ዕያየሽ ወጠምሻ፣
የሱን መድሃኒት፣
አርገሽ ለቀን ያዝሽው የኔን ማስታገሻ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
❤9😁9👍6
...........
ከመቅደስ ቆመን ነጠላ አዘቀዘቅን
ልንፈትንህ ብለን ትቢያ ላይ ወደቅን
አስቲ ከላህ ከዙፈንህ
ይሄን ድንጋይ ዳቦ አድርገው
ቃልህን ሳይሆን
የለት እንጀራ ነው ልጄ የሚያስፈልገው
በተጣበቀ አንጀት
በጎደለ ማጀት
እምነት ምን ይሰራል ተራራ የሚነቅል
ወንጌል ምን ይበጀል የማይሞላ ከቅል
ቀንቤሬ ቆፈሮ ማጭድ ከላረሰ
በሬ ተጠግርሮ ለምለም ካልጎረሰ
ጎደሎ ማጀቴን ድንጋይ ልሰግስገው
እውነት ካለህ ? ዳቦ አድርገው
ወንጌልህን ሳይሆን
የለት እንጀራ ነው ልጄ የሚያስፈልገው
ሰማይ እንደላም ጡት
ወተት ካዘነበ ከጸባኦት መንበር
ከትከሻ አውርጄ ሞፈርና ቀንበር
ነጠላ አዘቅዝቄ ከቤትህ ገደምኩኝ
ልፈትንህ ብዬ ከትቢያ ወደኩኝ
ካለህ አንድ ጠጠር
ወይ ጸጉሬን ባርከህ የሳምሶንን አርገው
የገፋኝን ሁሉ ዶግ አመድ ላድርገው
ወይ እሱም ካልሆነ
እምነት ሆኖኝ ጠጠር ወንጭፍ አብጅቼ
ዶሮ ላሳድበት ጎልያድ ትቼ
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
ከመቅደስ ቆመን ነጠላ አዘቀዘቅን
ልንፈትንህ ብለን ትቢያ ላይ ወደቅን
አስቲ ከላህ ከዙፈንህ
ይሄን ድንጋይ ዳቦ አድርገው
ቃልህን ሳይሆን
የለት እንጀራ ነው ልጄ የሚያስፈልገው
በተጣበቀ አንጀት
በጎደለ ማጀት
እምነት ምን ይሰራል ተራራ የሚነቅል
ወንጌል ምን ይበጀል የማይሞላ ከቅል
ቀንቤሬ ቆፈሮ ማጭድ ከላረሰ
በሬ ተጠግርሮ ለምለም ካልጎረሰ
ጎደሎ ማጀቴን ድንጋይ ልሰግስገው
እውነት ካለህ ? ዳቦ አድርገው
ወንጌልህን ሳይሆን
የለት እንጀራ ነው ልጄ የሚያስፈልገው
ሰማይ እንደላም ጡት
ወተት ካዘነበ ከጸባኦት መንበር
ከትከሻ አውርጄ ሞፈርና ቀንበር
ነጠላ አዘቅዝቄ ከቤትህ ገደምኩኝ
ልፈትንህ ብዬ ከትቢያ ወደኩኝ
ካለህ አንድ ጠጠር
ወይ ጸጉሬን ባርከህ የሳምሶንን አርገው
የገፋኝን ሁሉ ዶግ አመድ ላድርገው
ወይ እሱም ካልሆነ
እምነት ሆኖኝ ጠጠር ወንጭፍ አብጅቼ
ዶሮ ላሳድበት ጎልያድ ትቼ
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
❤29👍17🔥4👎3
............
ይሁን ካልሽ .....
ይሁን በቃ ትቼዋለው
ልብ ካልወደደ
ይቅር ማለት ምን ዋጋ አለው
ባትነግሪኝም ........
የገፋሽን ጥፋት
አብሮ መሆን ደርሶ ነፍስሽን ካስከፋት
ቃል እየመረኩኝ አልሻም ላባብል
ፊደል እያቀናው ስህተቴን ላስታብል
ይሁን ካልሽ
ይቅር ካልሽ
ይቅር በቃ ትቼዋለው
ልብ ካልወደደ
አብሮ መሆን ምን ዋጋ አለው
መነጣጠል ቢያረክስም
ፍቅርሽን አልከስም
ባትነግሪኝ አውቀዋለው
ኩርፊያሽ ሀቅ እንዳለው
ይቅር ብለሽ
በቃ ብለሽ
መለየት ከመረጥሽ መኖር ተነጥለሽ
ምን እላለው
ልብ ካልወደደ
አብሮ መሆን ምን ዋጋ አለው
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ይሁን ካልሽ .....
ይሁን በቃ ትቼዋለው
ልብ ካልወደደ
ይቅር ማለት ምን ዋጋ አለው
ባትነግሪኝም ........
የገፋሽን ጥፋት
አብሮ መሆን ደርሶ ነፍስሽን ካስከፋት
ቃል እየመረኩኝ አልሻም ላባብል
ፊደል እያቀናው ስህተቴን ላስታብል
ይሁን ካልሽ
ይቅር ካልሽ
ይቅር በቃ ትቼዋለው
ልብ ካልወደደ
አብሮ መሆን ምን ዋጋ አለው
መነጣጠል ቢያረክስም
ፍቅርሽን አልከስም
ባትነግሪኝ አውቀዋለው
ኩርፊያሽ ሀቅ እንዳለው
ይቅር ብለሽ
በቃ ብለሽ
መለየት ከመረጥሽ መኖር ተነጥለሽ
ምን እላለው
ልብ ካልወደደ
አብሮ መሆን ምን ዋጋ አለው
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
❤36👍28😢9🤩4
አታውቂም
(kerim
የተዋቡ አይኖችሽ ካልተፋብኝ እቶን
አፍሽ ካልጠራብኝ የርግማን መዓቱን
በዚህ ሁሉ መሀል
መዓዛሽን ካልማግኩት
ታድያ ምኑን ኖርኩት?
-
-
-
አለም ብትጠፋ
ካንቺ እጦት አይከፋ
አታውቂም
መኖርሽ እንደሚያኖረኝ
አታውቂም
ከሌላም አይቼሽ ደስታ እንደሚያሰክረኝ
ከኔ ደስታ ይልቅ ስለ አንቺ ደስታ
የልቤ መሻት ነው ስላንቺ አዬመታ
አላውቅም
ቅናት ይሉት ስሜት ወዴት ተሰወረ
ልቤስ ስለ እጦቱ ስለምን ታተረ?
(እንዳልኩሽ አላውቅም)
By @poem2513
@getem
@getem
@paappii
(kerim
የተዋቡ አይኖችሽ ካልተፋብኝ እቶን
አፍሽ ካልጠራብኝ የርግማን መዓቱን
በዚህ ሁሉ መሀል
መዓዛሽን ካልማግኩት
ታድያ ምኑን ኖርኩት?
-
-
-
አለም ብትጠፋ
ካንቺ እጦት አይከፋ
አታውቂም
መኖርሽ እንደሚያኖረኝ
አታውቂም
ከሌላም አይቼሽ ደስታ እንደሚያሰክረኝ
ከኔ ደስታ ይልቅ ስለ አንቺ ደስታ
የልቤ መሻት ነው ስላንቺ አዬመታ
አላውቅም
ቅናት ይሉት ስሜት ወዴት ተሰወረ
ልቤስ ስለ እጦቱ ስለምን ታተረ?
(እንዳልኩሽ አላውቅም)
By @poem2513
@getem
@getem
@paappii
❤32👍20👎1🔥1😢1
ድንገት ያገኘሁት የድሮ ግጥሜ
____
ጀምበር ገባች ፥ መሸ
ያጸዳሁት ቤቴም ፥ መልሶ ቆሸሸ
አልጠፋም መብራቱ
አልተበላም 'ራቱ
አሁንም ክፍት ነው በርና መስኮቱ ።
ለቁር ተጋለጠ ፥ ጓዳዬ እንደ ውጪው
መቼ ነው የምትመጪው ?
መጽሐፍ ገለጥኩና መልሼ ዘጋሁት
ልጽፍ አሰብኩና ብዕሬን ወረወርኩት
መቆም መንጎራደድ
መቆም መንጎራደድ
መቆዘም መተከዝ ፥ በሐሳብ መሰደድ
ደርሶ ብንን ብንን
ደሞ ቁጭ ብድግ
ካንቺ ውጭ አላውቅም ምን እንደምፈልግ ።
ምኞት ነው ያለኝ ፥ ዝም ብሎ ምኞት
ወይ የማያኖር ፥ ወይ የማያስሞት
ትመጫለሽ እያልኩ በጉጉት ከምኖር
ምናለ በሞትኩኝ ለአንድ ለስድስት ወር ።
@getem
@getem
@paappii
By Hab Hd
____
ጀምበር ገባች ፥ መሸ
ያጸዳሁት ቤቴም ፥ መልሶ ቆሸሸ
አልጠፋም መብራቱ
አልተበላም 'ራቱ
አሁንም ክፍት ነው በርና መስኮቱ ።
ለቁር ተጋለጠ ፥ ጓዳዬ እንደ ውጪው
መቼ ነው የምትመጪው ?
መጽሐፍ ገለጥኩና መልሼ ዘጋሁት
ልጽፍ አሰብኩና ብዕሬን ወረወርኩት
መቆም መንጎራደድ
መቆም መንጎራደድ
መቆዘም መተከዝ ፥ በሐሳብ መሰደድ
ደርሶ ብንን ብንን
ደሞ ቁጭ ብድግ
ካንቺ ውጭ አላውቅም ምን እንደምፈልግ ።
ምኞት ነው ያለኝ ፥ ዝም ብሎ ምኞት
ወይ የማያኖር ፥ ወይ የማያስሞት
ትመጫለሽ እያልኩ በጉጉት ከምኖር
ምናለ በሞትኩኝ ለአንድ ለስድስት ወር ።
@getem
@getem
@paappii
By Hab Hd
❤73👍34😁26🤩7😢4
............
ትከተይኛለሽ ብዬ ስለማስብ
በሄድኩበት ሁሉ እጅ እንድሰበስብ
መዞር እፈራለሁ
ዞሬ ያጣሁሽ እንደው
ብቻዬን መሆኔስ ምን ነጻነት አለው
ትከተይኛለሽ
በአለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማስብ
ትዝታ እንደ ገላ ይዳብሰኝና
አለሄደችም ብዬ
ልቤን አጽና..ና...ና
ጀርባዬን አምናለሁ
አንቺ ከነጠቀኝ
እውነት ምን ዋጋ አለው
ያልኖሩበት ነገ ተስፋው ምን ሊጠቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቀም
በሄድኩበት ሁሉ
በሳር በገደሉ
እረኛ ያጣ በሬ በኮቴው ሲያደቀው
አንቺን ነሽ በዬ ነው በተስፈ የምስቀው
ጠረንሽ ቢጠፋኝ
ሽቶ ያኮፈሳት ላባም ሴት ፈልጌ
በሴሰኛ ስሜት ጭኗን ተፋትጌ
ሲረካ መንፈሴ
አንቺ ነሽ ብሎ ነው
የሚስቀው ጥርሴ
መቼም ለመኮነን
መዞርም አያሻም ሀጥያት በዝቷል ከፊት
የከፋኝ ጊዜ ነው የማቀው ያንቺን ፊት
ትከተይኛለሽ
ባለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማምን
እንትን ተመኝቼ ጌታዬን ስለምን
የሷንም እላለው
ይሰማሽ እንደሆን
እንጃ ምን አውቃለሁ
መሄድ እንደቀላል
መንገዱን ሲያረዝመው
መድረስ አይናፍቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቅም
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
ትከተይኛለሽ ብዬ ስለማስብ
በሄድኩበት ሁሉ እጅ እንድሰበስብ
መዞር እፈራለሁ
ዞሬ ያጣሁሽ እንደው
ብቻዬን መሆኔስ ምን ነጻነት አለው
ትከተይኛለሽ
በአለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማስብ
ትዝታ እንደ ገላ ይዳብሰኝና
አለሄደችም ብዬ
ልቤን አጽና..ና...ና
ጀርባዬን አምናለሁ
አንቺ ከነጠቀኝ
እውነት ምን ዋጋ አለው
ያልኖሩበት ነገ ተስፋው ምን ሊጠቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቀም
በሄድኩበት ሁሉ
በሳር በገደሉ
እረኛ ያጣ በሬ በኮቴው ሲያደቀው
አንቺን ነሽ በዬ ነው በተስፈ የምስቀው
ጠረንሽ ቢጠፋኝ
ሽቶ ያኮፈሳት ላባም ሴት ፈልጌ
በሴሰኛ ስሜት ጭኗን ተፋትጌ
ሲረካ መንፈሴ
አንቺ ነሽ ብሎ ነው
የሚስቀው ጥርሴ
መቼም ለመኮነን
መዞርም አያሻም ሀጥያት በዝቷል ከፊት
የከፋኝ ጊዜ ነው የማቀው ያንቺን ፊት
ትከተይኛለሽ
ባለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማምን
እንትን ተመኝቼ ጌታዬን ስለምን
የሷንም እላለው
ይሰማሽ እንደሆን
እንጃ ምን አውቃለሁ
መሄድ እንደቀላል
መንገዱን ሲያረዝመው
መድረስ አይናፍቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቅም
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
👍40❤25🔥4😢1
ስርአት!
(የሞገሤ ልጅ)
አንተ የእኔ ምትክ፣
የእራሴ መታያ የአብራኬ ክፋይ፣
እንኳንም ወለድኩህ፣
የፈጠረህ ፈቅዶ ዐይኔን በዐይኔ እንዳይ።
አንተ ግን ቸኩለህ፣
መልሰህ መሄድህ ወደመጣህበት፣
ምን ሰይጣን መክሮህ ነው፣
ያረከኝ በሃዘን እንድኮረማመት።
የውልህ ልንገርህ፣
ተወልዶ ማረፉ በሰላሳኛ ቀን፣
ላንተም ኪሳራ ነው፣
ለኔም የእድሜ ልክ ስብራት ሰቀቀን።
ያንተን ጉዳት ላርዳህ፣
ለገነት ከሆነ ሞትህ በዚህ እድሜ፣
እኔም አልገባሁም፣
ካንተ በላይ ኖሬ 55 ቀን ጾሜ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
(የሞገሤ ልጅ)
አንተ የእኔ ምትክ፣
የእራሴ መታያ የአብራኬ ክፋይ፣
እንኳንም ወለድኩህ፣
የፈጠረህ ፈቅዶ ዐይኔን በዐይኔ እንዳይ።
አንተ ግን ቸኩለህ፣
መልሰህ መሄድህ ወደመጣህበት፣
ምን ሰይጣን መክሮህ ነው፣
ያረከኝ በሃዘን እንድኮረማመት።
የውልህ ልንገርህ፣
ተወልዶ ማረፉ በሰላሳኛ ቀን፣
ላንተም ኪሳራ ነው፣
ለኔም የእድሜ ልክ ስብራት ሰቀቀን።
ያንተን ጉዳት ላርዳህ፣
ለገነት ከሆነ ሞትህ በዚህ እድሜ፣
እኔም አልገባሁም፣
ካንተ በላይ ኖሬ 55 ቀን ጾሜ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
😢32👍23❤8👎3😱2
..........
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የቸረች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በነጭና ጥቁር
በበዛበት ህይወት
ተፈጥሮን በረሳ ቀለም በናፈቀው
ጸሀይ አይደለችም
ገላሽን አቅፎ ነው ጓዳዬ የሞቀው
ቤቴ የደመቀው
ያልተጋሩት እቶን
የሚማገዱበት ልክ እንደ ዕሳት ዕራት
ሞቶ የመኖር ብስራት
በብርሀኗ ውስጥ በሚንቦገቦገው
ፍቅርን ልፈልገው
ስዳራሽ እያዩ
ሞቶ ነው እያሉ ህያዋን ሲለዩ
ለዚህ ነው የምልሽ
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የሰጠች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በሳት ላልተዳሩ
ላልተፋቀሩ!
ቅሉ አይገባቸውም የቀለም አደሱ
የፍቅራቸው ምሱ ?
ዕሳት ዕራት መሆን ጸጋ መች ታደለ
ከሚነድ ወላፈን ጠብታን ያከለ
ለዕሳት ነፍስ የዘራ ስጋውን ሰውቶ
ጸሀይ አይደለችም
ውበቷ ብቻ ነው የሚታየው ጎልቶ
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የቸረች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በነጭና ጥቁር
በበዛበት ህይወት
ተፈጥሮን በረሳ ቀለም በናፈቀው
ጸሀይ አይደለችም
ገላሽን አቅፎ ነው ጓዳዬ የሞቀው
ቤቴ የደመቀው
ያልተጋሩት እቶን
የሚማገዱበት ልክ እንደ ዕሳት ዕራት
ሞቶ የመኖር ብስራት
በብርሀኗ ውስጥ በሚንቦገቦገው
ፍቅርን ልፈልገው
ስዳራሽ እያዩ
ሞቶ ነው እያሉ ህያዋን ሲለዩ
ለዚህ ነው የምልሽ
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የሰጠች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በሳት ላልተዳሩ
ላልተፋቀሩ!
ቅሉ አይገባቸውም የቀለም አደሱ
የፍቅራቸው ምሱ ?
ዕሳት ዕራት መሆን ጸጋ መች ታደለ
ከሚነድ ወላፈን ጠብታን ያከለ
ለዕሳት ነፍስ የዘራ ስጋውን ሰውቶ
ጸሀይ አይደለችም
ውበቷ ብቻ ነው የሚታየው ጎልቶ
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍27❤16🔥3
በየሰፈሩ ሰፍረን
በየአጥሩ ተንጠልጠለን
አድዋን ያህል
አድባር ጥለን
ካምና ርቀን
ዛሬን ንቀን
ነገን ናፍቀን
መራመዱ እየጨነቀን
በየጥጉ ተናንቀን
ቀኑን ማሰብ እስኪያስፈራው
የታለ ባለፈረሱ?
የታለ ባለ ባንዴራው?
የታል የትውልድ አደራው?
አድዋን ያህል ትልቅ ጥለት
አድዋን ያህል ህብር ቀለም
ክብሩ ገብቶን
ፍሬው ታይቶን
ሳንደምቅበት ተያይዘን
ሳንኮራበት ታሪክ መዘን
በጊዜ ፊት እንዲህ ፈዘን
ያከበረን ያስከበረን
ኩራት ሆኖ ያዘለቀን
አድዋ ያህል ዘ ላ ለ ም ቀን
ስሙን መጥራት
ድሉን ማሰብ ተናነቀን?!
By Thomas lemma
@getem
@getem
@paappii
በየአጥሩ ተንጠልጠለን
አድዋን ያህል
አድባር ጥለን
ካምና ርቀን
ዛሬን ንቀን
ነገን ናፍቀን
መራመዱ እየጨነቀን
በየጥጉ ተናንቀን
ቀኑን ማሰብ እስኪያስፈራው
የታለ ባለፈረሱ?
የታለ ባለ ባንዴራው?
የታል የትውልድ አደራው?
አድዋን ያህል ትልቅ ጥለት
አድዋን ያህል ህብር ቀለም
ክብሩ ገብቶን
ፍሬው ታይቶን
ሳንደምቅበት ተያይዘን
ሳንኮራበት ታሪክ መዘን
በጊዜ ፊት እንዲህ ፈዘን
ያከበረን ያስከበረን
ኩራት ሆኖ ያዘለቀን
አድዋ ያህል ዘ ላ ለ ም ቀን
ስሙን መጥራት
ድሉን ማሰብ ተናነቀን?!
By Thomas lemma
@getem
@getem
@paappii
👍39❤32🔥8😢3🤩1
"ድንቄም ቆራጭ"😁😁😁
"""""""""""""""""""""
ከልብ ተሠርንቆ ልውጣ አልውጣ እያለ፤
ያስገባንው ነገር ከአቅም ካየ"ለ።
ይውጣ ምናባቱ ልብን ከበሽተ ካላረገን ደህና፤
አንቅሮ መትፋት ነው ከሚያሳጣን ጤና።
ሰውም እንደዚህ ነው፥
የልባችን እሳት የልባችን ንዳድ ለሱ ከበረደው፤
የፍቅራችን ሙቀት ቀዝቅዞ ከታየው።
ምን ሊያረግ ይቀመጥ ሊሆነን ፈተና፤
ከተመቸው ይሂድ መንገዱ ያውና።
የልባችን መሻት መሻቱ ካልሆነ፤
የመውደድ ፍላቱ ከሱው ከተነነ።
ልቡ የሸፈተን አስረን ላናስቀረው፤
መንገዱ ያውና ይሂድ ከተመቸው።
ብዬ እፎክርና ዝቼ በሃሳቤ፤
አስሮ ያስቀመጠው ይሸነፋል ልቤ።
አድሮ ልመና...ተው ፍታኝ
የቃልህ እስረኛ ነኝ🥹
ምን ላርግ ከእኔ ዘንድ አልሰራም
✍ጦቢያ
ቀን 21
የካቲት፦2017-አርብ
@getem
@getem
@getem
"""""""""""""""""""""
ከልብ ተሠርንቆ ልውጣ አልውጣ እያለ፤
ያስገባንው ነገር ከአቅም ካየ"ለ።
ይውጣ ምናባቱ ልብን ከበሽተ ካላረገን ደህና፤
አንቅሮ መትፋት ነው ከሚያሳጣን ጤና።
ሰውም እንደዚህ ነው፥
የልባችን እሳት የልባችን ንዳድ ለሱ ከበረደው፤
የፍቅራችን ሙቀት ቀዝቅዞ ከታየው።
ምን ሊያረግ ይቀመጥ ሊሆነን ፈተና፤
ከተመቸው ይሂድ መንገዱ ያውና።
የልባችን መሻት መሻቱ ካልሆነ፤
የመውደድ ፍላቱ ከሱው ከተነነ።
ልቡ የሸፈተን አስረን ላናስቀረው፤
መንገዱ ያውና ይሂድ ከተመቸው።
ብዬ እፎክርና ዝቼ በሃሳቤ፤
አስሮ ያስቀመጠው ይሸነፋል ልቤ።
አድሮ ልመና...ተው ፍታኝ
የቃልህ እስረኛ ነኝ🥹
ምን ላርግ ከእኔ ዘንድ አልሰራም
✍ጦቢያ
ቀን 21
የካቲት፦2017-አርብ
@getem
@getem
@getem
👍44❤16