እናንተ የምወድዳችኹ ፤
ስነ-ፅሁፍን የምትወድዱ ፤
የግጥም ነፍስ ያላችኹ ፤
ወንድሞቼ ፤ እህቶቼ ፤ ወዳጆቼ ፤ ታላላቆቼ እና በደስታዬ ደስ የሚላችኹ የዘመን ተጋሪዎቼ ኹሉ ፤ ይቺን የመጀመሪያ ስራዬን ቅድሚያ ገዝታችሁ ፤ ከጓዳ ወደ አደባባይ እንድትሸኙልኝ ስል ፤ የተወደደ የወዳጅነት ግብዣዬን እጋብዛችዃለሁ ።
ከወዲኹ ...
እጅግ እጅግ አመሰግናችዃለሁኝ
ኑሩልኝ !
ቴዎድሮስ ካሳ
____
የመፅሐፍ ቅድመ ሽያጭ ማስታወቂያ
Reserve yours now—it's on pre-order!
ርዕስ /Title - የዱር አበባ / Wild Flower
ዘርፍ / Genres - ስነ-ግጥም /Poetry
ዋጋ/ price - 300 ብር/ birr
የባንክ ቁጥር / Bank Accounts :
ቴዎድሮስ ካሳው አስረሴ
Tewodros Kassaw Asresse
ንግድ ባንክ / CBE - 1000360039847 ወይም 1000292025185 (ናትናኤል እሸቱ)
አዋሽ ባንክ /Awash Bank - 01320885596200
ሲቢኢ ብር / CBE Birr - 0972338625
ቴሌብር/ Tellebirr - 0972338625
[ ማሳሰብያ : ዃላ ለማስታወሻ ይረዳኝ ዘንድ Screenshot አንስታችሁ በውስጥ በሜሴንጀሬ አልያም በቴሌግራም አድራሻዬ @Poet_tedi መላኩን እንዳትረሱት ይሁን ።]
ስነ-ፅሁፍን የምትወድዱ ፤
የግጥም ነፍስ ያላችኹ ፤
ወንድሞቼ ፤ እህቶቼ ፤ ወዳጆቼ ፤ ታላላቆቼ እና በደስታዬ ደስ የሚላችኹ የዘመን ተጋሪዎቼ ኹሉ ፤ ይቺን የመጀመሪያ ስራዬን ቅድሚያ ገዝታችሁ ፤ ከጓዳ ወደ አደባባይ እንድትሸኙልኝ ስል ፤ የተወደደ የወዳጅነት ግብዣዬን እጋብዛችዃለሁ ።
ከወዲኹ ...
እጅግ እጅግ አመሰግናችዃለሁኝ
ኑሩልኝ !
ቴዎድሮስ ካሳ
____
የመፅሐፍ ቅድመ ሽያጭ ማስታወቂያ
Reserve yours now—it's on pre-order!
ርዕስ /Title - የዱር አበባ / Wild Flower
ዘርፍ / Genres - ስነ-ግጥም /Poetry
ዋጋ/ price - 300 ብር/ birr
የባንክ ቁጥር / Bank Accounts :
ቴዎድሮስ ካሳው አስረሴ
Tewodros Kassaw Asresse
ንግድ ባንክ / CBE - 1000360039847 ወይም 1000292025185 (ናትናኤል እሸቱ)
አዋሽ ባንክ /Awash Bank - 01320885596200
ሲቢኢ ብር / CBE Birr - 0972338625
ቴሌብር/ Tellebirr - 0972338625
[ ማሳሰብያ : ዃላ ለማስታወሻ ይረዳኝ ዘንድ Screenshot አንስታችሁ በውስጥ በሜሴንጀሬ አልያም በቴሌግራም አድራሻዬ @Poet_tedi መላኩን እንዳትረሱት ይሁን ።]
👍23🔥6❤5
# ይድረስ ለጨረቃ #
እንዴት ነሽ ጨረቃ
እንዴትነሽ በሰማይ
ምን ይታይሻል
ምን አለ ምድር ላይ… ?
በየጉራንጉሩ ሰው ነውሩን ደብቆ
የሚሰራው ስራ ህሌናውን ሰርቆ
ይታይሽ ከሆነ ሴራ ሲጎነጎን
የመከራ ጎጆ ሲሰራ ሲጠግን
የክፋት እንጀራ ሲቦካ ሲጋገር
የልቦና ቁስል ሲማገር ሲታጠር
ንገሪኝ በሞቴ ይገለጥ ጉዱ
የሰውልጅ ዶሴ የበደል ሰነዱ
እኔም ልናገር ልመስክር ለፍርዱ ።
@topazionnn
@getem
@getem
እንዴት ነሽ ጨረቃ
እንዴትነሽ በሰማይ
ምን ይታይሻል
ምን አለ ምድር ላይ… ?
በየጉራንጉሩ ሰው ነውሩን ደብቆ
የሚሰራው ስራ ህሌናውን ሰርቆ
ይታይሽ ከሆነ ሴራ ሲጎነጎን
የመከራ ጎጆ ሲሰራ ሲጠግን
የክፋት እንጀራ ሲቦካ ሲጋገር
የልቦና ቁስል ሲማገር ሲታጠር
ንገሪኝ በሞቴ ይገለጥ ጉዱ
የሰውልጅ ዶሴ የበደል ሰነዱ
እኔም ልናገር ልመስክር ለፍርዱ ።
@topazionnn
@getem
@getem
❤41👍29🔥8😁1
እኔ ያንቺ አለም
ደብዘዝ የምል ደማቅ ቀለም
የምተጋ ነገን ማልም
ለኔም ላንቺም የምሆን ህልም
ተዛምደናል ኪዳን መተን
መሃላችን ለቃል ሰተን
ነበርሽ የኔ ብርቱ ወገን
ጥንካሬሽ አንድ ያረገን
ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
የሄድሽበት ከኔ ይርቃል
ረስተሻል መሃላ ቃል
የኔ ገላ ያልታደለ
አንቺን ልኮ ባዶ አደረ
ደህና አድሯል ወይ ያንቺ ገላ
ባሉን ትቶ የተዳራ
ሽሎሽ ነው ወይ ከኔ እሱን
ቃል ማሃላን ማፋረሱን
ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
አንድን ይዞ ሳይራቡ
ምን ይሉታል መደረቡ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ደብዘዝ የምል ደማቅ ቀለም
የምተጋ ነገን ማልም
ለኔም ላንቺም የምሆን ህልም
ተዛምደናል ኪዳን መተን
መሃላችን ለቃል ሰተን
ነበርሽ የኔ ብርቱ ወገን
ጥንካሬሽ አንድ ያረገን
ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
የሄድሽበት ከኔ ይርቃል
ረስተሻል መሃላ ቃል
የኔ ገላ ያልታደለ
አንቺን ልኮ ባዶ አደረ
ደህና አድሯል ወይ ያንቺ ገላ
ባሉን ትቶ የተዳራ
ሽሎሽ ነው ወይ ከኔ እሱን
ቃል ማሃላን ማፋረሱን
ያሳዝናል ጊዜሽ እቱ
ተዛምደሻል ከማዕቱ
አንድን ይዞ ሳይራቡ
ምን ይሉታል መደረቡ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍53❤11😢3🔥2😱2🎉1
እልፍ ስትል እልፍ አበሳ ሄድ ስትል ጉድ ጭካኔ በመንገድህ ለሚነጉደው
ምን ለማትረፍ ምን ለማግኘት እርምጃህን 'ምትቀጥለው
ወዴት ይሆን ህይወቴ ሆይ የምትሄደው
የብቻነት የስቃይ ቤት ምን ይሆን ‘ምትፈልገው
እዚህ የእንባ ጎርፍ ውስጥ አለምን ከሰራት
ብትሰምጥ ብትሞት እርሷን እንደው ይቸግራት?
ደስታ ፍለጋ ‘ምትባዝን ህይወቴ ሆይ
ከንቱነት ነው አንተን ‘ሚቆይ
አንተ አበባው በሜዳህ ላይ የምትስቀው
አንቺም ወፏ ከዛፍሽ ስር ተደብቀሽ 'ምታለቅሺው
ፍፃሜያቹ ለካ አንድ ነው
ለማይዘገን ጥቂት ደስታ ዞሮ እንደ ጉም ለሚበነው
በስለቱ በጫፉ ላይ አየዘለልክ 'ምትጨፍረው
.....አንተ እኮ ነህ የምትደንቀው
Translated from "hymen of death " the movie
By yodan
@getem
@getem
@getem
ምን ለማትረፍ ምን ለማግኘት እርምጃህን 'ምትቀጥለው
ወዴት ይሆን ህይወቴ ሆይ የምትሄደው
የብቻነት የስቃይ ቤት ምን ይሆን ‘ምትፈልገው
እዚህ የእንባ ጎርፍ ውስጥ አለምን ከሰራት
ብትሰምጥ ብትሞት እርሷን እንደው ይቸግራት?
ደስታ ፍለጋ ‘ምትባዝን ህይወቴ ሆይ
ከንቱነት ነው አንተን ‘ሚቆይ
አንተ አበባው በሜዳህ ላይ የምትስቀው
አንቺም ወፏ ከዛፍሽ ስር ተደብቀሽ 'ምታለቅሺው
ፍፃሜያቹ ለካ አንድ ነው
ለማይዘገን ጥቂት ደስታ ዞሮ እንደ ጉም ለሚበነው
በስለቱ በጫፉ ላይ አየዘለልክ 'ምትጨፍረው
.....አንተ እኮ ነህ የምትደንቀው
Translated from "hymen of death " the movie
By yodan
@getem
@getem
@getem
👍33❤9🔥1😢1
ተራራ የሆነብንን የዳህንበትን አቀበት
እየናጠጡ እየፈረጠጡ ተንደረደሩበት
መስከኛ ያለውን ለም መሬት
ፎሮሹ ፈጩበት
ወቁ ሰለቁበት
አደራ አማን ብለን ሳለ
አልተዘገረ
አልተመተረ
ከተባለ
አኑር ጠብቀን ብለን ሳለ
ከሆነ የሞት ሹም
አይሳሉ ስለት ለሞታችን የተሳለ
ተመርቆለትም ከኪሎው ካለየ
ወደ ተመዛኙ ካላዘነበለ
አይጠረጥርም ወይ
ምንም ያልጠየቀ ?
ክሳት ገፅ የለውም
አጥንት ካልገለጠ ?
ነገር ነገሩን ቢለይም
ምኑን ከምኑ
ውል ያልያዘ ሰው
ቢመሽበትም አይነጋለትም
ዘንድሮም ዘንድሮ ተባለ
ሹም ሽረቱ ፍርዱም ተሻረ
ውሸቱ ሲፍም እውነት ከሰመ
ጊዜ ለሁሉ መልስ ቢያኖርም
ምኑን ከምኑ
ውል የተሳተው
ቢመሽበትም አይነጋለትም
By mik
@getem
@getem
@paappii
እየናጠጡ እየፈረጠጡ ተንደረደሩበት
መስከኛ ያለውን ለም መሬት
ፎሮሹ ፈጩበት
ወቁ ሰለቁበት
አደራ አማን ብለን ሳለ
አልተዘገረ
አልተመተረ
ከተባለ
አኑር ጠብቀን ብለን ሳለ
ከሆነ የሞት ሹም
አይሳሉ ስለት ለሞታችን የተሳለ
ተመርቆለትም ከኪሎው ካለየ
ወደ ተመዛኙ ካላዘነበለ
አይጠረጥርም ወይ
ምንም ያልጠየቀ ?
ክሳት ገፅ የለውም
አጥንት ካልገለጠ ?
ነገር ነገሩን ቢለይም
ምኑን ከምኑ
ውል ያልያዘ ሰው
ቢመሽበትም አይነጋለትም
ዘንድሮም ዘንድሮ ተባለ
ሹም ሽረቱ ፍርዱም ተሻረ
ውሸቱ ሲፍም እውነት ከሰመ
ጊዜ ለሁሉ መልስ ቢያኖርም
ምኑን ከምኑ
ውል የተሳተው
ቢመሽበትም አይነጋለትም
By mik
@getem
@getem
@paappii
👍32❤8🔥1
ጭጋጉ ሲያከትም በክረምቱ ማብቂያ፤
ፀሐይ ስትፈነጥቅ በመሬት መድረቂያ፤
የፀደይ አበባ ማበብ ስትጀምር ፤
አደይዋ ለሰዎች ተስፋን ስታበስር፤
በወርሐ ጥቅምት በመጀመሪያው ቀን፤
ዛሬን ነዉ የወጣሁ ከእናቴ ማኅፀን።
ያቺ እናቴ በጭንቋ ቀን ምጧ ደርሶ፤
እያነባች ላብ አጥምቋት ፊቷ ርሶ፤
ማርያም ማርያም እያለች፤
ምጧ ቀለለላት ስሟን እየጠራች።
በልደቷ ቀን መታሰቢያ.........
ሰምታ ጸሎት ስዕለቷን፤
ማርያም ማረቻት እናቴን።
በዚያች ሴኮንድ በዚያች ቅፅበት........
ከልቤ ታትሞ ማርያም የሚለው ስም፤
ለዛሬ ደረስኩኝ በፍቅሯ ስሸለም።
የእቅፏን መዓዛ እየመገበችኝ፤
የትህትናን ዋጋ እያስተማረችኝ፤
የልጇን ጌትነት በልቤ ሰሌዳ፤
የእርሷን ትሁትነት በፍቅር አዋድዳ፤
የንስሐ እድሜን ፈጥና አሰጠችኝ፤
አዲስ ቀንን እንዳይ ድንግል ባረከችኝ።
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎊🎊🎊🎊
ዔደን_ታደሰ @ediwub
ጥቅምት ፩/፳፻፲፯
መልካም ልደት ለእኔ🎂🎂🎊🎊🎊
@getem
@getem
@getem
ፀሐይ ስትፈነጥቅ በመሬት መድረቂያ፤
የፀደይ አበባ ማበብ ስትጀምር ፤
አደይዋ ለሰዎች ተስፋን ስታበስር፤
በወርሐ ጥቅምት በመጀመሪያው ቀን፤
ዛሬን ነዉ የወጣሁ ከእናቴ ማኅፀን።
ያቺ እናቴ በጭንቋ ቀን ምጧ ደርሶ፤
እያነባች ላብ አጥምቋት ፊቷ ርሶ፤
ማርያም ማርያም እያለች፤
ምጧ ቀለለላት ስሟን እየጠራች።
በልደቷ ቀን መታሰቢያ.........
ሰምታ ጸሎት ስዕለቷን፤
ማርያም ማረቻት እናቴን።
በዚያች ሴኮንድ በዚያች ቅፅበት........
ከልቤ ታትሞ ማርያም የሚለው ስም፤
ለዛሬ ደረስኩኝ በፍቅሯ ስሸለም።
የእቅፏን መዓዛ እየመገበችኝ፤
የትህትናን ዋጋ እያስተማረችኝ፤
የልጇን ጌትነት በልቤ ሰሌዳ፤
የእርሷን ትሁትነት በፍቅር አዋድዳ፤
የንስሐ እድሜን ፈጥና አሰጠችኝ፤
አዲስ ቀንን እንዳይ ድንግል ባረከችኝ።
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎊🎊🎊🎊
ዔደን_ታደሰ @ediwub
ጥቅምት ፩/፳፻፲፯
@getem
@getem
@getem
❤68🎉27👍24🤩4
...ትዝታ
ትዝታ ገዳዩ ናፍቆትን ያብሳል
በጥላቻ መሀል ፍቅርን ይሰብካል
እንባን አሳብሶ በምናብ ይወስዳል
ትዝታ ከባዱ ቫይረስ ነው ይገላል
By
@Hanipia
@getem
@getem
@Hanipiagetem
ትዝታ ገዳዩ ናፍቆትን ያብሳል
በጥላቻ መሀል ፍቅርን ይሰብካል
እንባን አሳብሶ በምናብ ይወስዳል
ትዝታ ከባዱ ቫይረስ ነው ይገላል
By
@Hanipia
@getem
@getem
@Hanipiagetem
👍37❤3👎2🔥1😱1😢1🤩1
ሰው ፈለገች የሚያፅናናት
ችግር ውስጧን ሚረዳላት
ሰው ፈለገች የሚያፅናናት
የአይኗን እንባ ሚያብስላት
ለጠየኳት ጥያቄዎች
ምንም ነበር መልሰ ቃሏ
ብዙ እንደሆነች ግን
ይናገራል ፊት አካሏ
ብቻ...ዝም ብላለች
ታስታውቃለች ሆድ ብሷታል
ታስታውቃለች እንደከፋት
ቆንጆ መልኳን ተመልክቶ
ማን ይሆን ሰው ደርሶ የገፋት
ደረቅ ብሏል ውብ ከንፈሯ
አላገኘም አንዳች እህል
ቀዝቀዝ ብሏል የእጇ መዳፍ
ምን ሁናለች እቺ ጉብል
ቀና ብላ እያየችኝ
ዘረገፈች የአይኗን እንባ
ስቅስቅ ብላ አለቀሰች
ነጠላ እጇን ተከናንባ
እንዲህ ነው እያለች መናገር ባትችልም የውስጧን አውጥታ
ብዙ አውርታኛለች ከኔ ጋራ ሳለች ቃሏን በዝምታ
ይገርማል አንዳንዴ
ቃላት ሳይደረደር ምስክር ሳይጠራ ሀቀኛ ሳይለካ
ብዙ ሳንናገር በዝምታ ብቻ ቃል ይወጣል ለካ!
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ችግር ውስጧን ሚረዳላት
ሰው ፈለገች የሚያፅናናት
የአይኗን እንባ ሚያብስላት
ለጠየኳት ጥያቄዎች
ምንም ነበር መልሰ ቃሏ
ብዙ እንደሆነች ግን
ይናገራል ፊት አካሏ
ብቻ...ዝም ብላለች
ታስታውቃለች ሆድ ብሷታል
ታስታውቃለች እንደከፋት
ቆንጆ መልኳን ተመልክቶ
ማን ይሆን ሰው ደርሶ የገፋት
ደረቅ ብሏል ውብ ከንፈሯ
አላገኘም አንዳች እህል
ቀዝቀዝ ብሏል የእጇ መዳፍ
ምን ሁናለች እቺ ጉብል
ቀና ብላ እያየችኝ
ዘረገፈች የአይኗን እንባ
ስቅስቅ ብላ አለቀሰች
ነጠላ እጇን ተከናንባ
እንዲህ ነው እያለች መናገር ባትችልም የውስጧን አውጥታ
ብዙ አውርታኛለች ከኔ ጋራ ሳለች ቃሏን በዝምታ
ይገርማል አንዳንዴ
ቃላት ሳይደረደር ምስክር ሳይጠራ ሀቀኛ ሳይለካ
ብዙ ሳንናገር በዝምታ ብቻ ቃል ይወጣል ለካ!
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍90❤50🔥9🎉3😁1😢1🤩1
ረክሶ ነው እንጂ
እግዜር ሚባል አልማዝ
ይሻማበት ነበር
ፍጡር እንደቁስ ጓዝ
ረክሳ ነው እንጂ
ማሪያም ሚሏት ሀምሎ
ቤት አያጣም ነበር
ልብ 'ሚባል ኪሎ
ቀንሶ ነው እንጂ
ሰው ሚባል ሳጥናኤል
ወንበሩን ባልሸጠው
ለእነ ሊቅ ሚካኤል
ቅዱስ ሚካኤልስ
ይጠብቃል ሰውን
ቅዱስ ገብርኤልስ
ያወጣል እሳትን
እግዜር ግን ዝም ነው
ያቺን ቀን ያላትን
ሀገር ሚባል ዕዳ
ቃል ሚያክል ሚካኤል
ሸጦታል አሉ ሰውን ለሳጥናኤል
እግዜሩ ቢረክስ ገነት ይወደዳል
ሳጥናኤል ቢረክስ ሲኦል ሰውን ያጣል
ሰው ሰውን ካጣ ሰው ከየት ይገባል ?
ጨለማው ላይ ሆነሽ
ስሜንም አትጥሪ
ጊዜ ሚጠብቅ ሰው
አይባልም ፈሪ
እባክሽን ዓለም
ባይሆን አምላክ ፍሪ
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
እግዜር ሚባል አልማዝ
ይሻማበት ነበር
ፍጡር እንደቁስ ጓዝ
ረክሳ ነው እንጂ
ማሪያም ሚሏት ሀምሎ
ቤት አያጣም ነበር
ልብ 'ሚባል ኪሎ
ቀንሶ ነው እንጂ
ሰው ሚባል ሳጥናኤል
ወንበሩን ባልሸጠው
ለእነ ሊቅ ሚካኤል
ቅዱስ ሚካኤልስ
ይጠብቃል ሰውን
ቅዱስ ገብርኤልስ
ያወጣል እሳትን
እግዜር ግን ዝም ነው
ያቺን ቀን ያላትን
ሀገር ሚባል ዕዳ
ቃል ሚያክል ሚካኤል
ሸጦታል አሉ ሰውን ለሳጥናኤል
እግዜሩ ቢረክስ ገነት ይወደዳል
ሳጥናኤል ቢረክስ ሲኦል ሰውን ያጣል
ሰው ሰውን ካጣ ሰው ከየት ይገባል ?
ጨለማው ላይ ሆነሽ
ስሜንም አትጥሪ
ጊዜ ሚጠብቅ ሰው
አይባልም ፈሪ
እባክሽን ዓለም
ባይሆን አምላክ ፍሪ
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
❤24👍19👎16🔥4😱1
የድሮው አምላክ
'
'
አዲሱ አምላክ ገና አልመጣም
የቀድሞ አምላክ አገናኜን ፣
ቢያንስ ቢያንስ ባያድሰን ፥
ለትዝታ እስኪፈጥረን ፥
አዲሱ አምላክ እስኪ ተወን ፣
'
'
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
'
'
አዲሱ አምላክ ገና አልመጣም
የቀድሞ አምላክ አገናኜን ፣
ቢያንስ ቢያንስ ባያድሰን ፥
ለትዝታ እስኪፈጥረን ፥
አዲሱ አምላክ እስኪ ተወን ፣
'
'
@geez_mulat
ግዕዝ ሙላት
@getem
@getem
@paappii
👍18❤8👎3🤩3🎉2😁1