#እግዜሩ ነው የሚገርመኝ
ምኞትን ያህል ነገር ተፈጥሮ ስትቸረኝ
በእጁ አበጃጅቶ የኳላትን እንስት ደጄ እያሳየኝ
አታመንዝር አለኝ!
.
እግዜሩ ነው የሚገርመኝ
በእሾህ በአሜኬላ ዓለሚቷን አጥሮ
አዳም ይብላ አለ በላቦቱ ግሮ።
እሺ የት እንስራ?
በዚም በዛም ያለው አለበት ደንቃራ
በቃ ልስረቅ ልንጠቅ
ቀን መሽቶ ቢያልፍልኝ...
እንዲህ አልል ነገር የርሱ ህግ አለብኝ።
.
እውነት!
እውነት!
እውነት!
እግዜሀር ነህ የምትገርመኝ
ድመት አርገህ ፈጥረህ ወተት አትንጠቀኝ
ነብር አርገህ ፈጥረህ ፍየል አትስረቀኝ
ስትለኝ...
እንደዚህ አትበለኝ...
ብዬም አልበሳጭ አልሳደብ ነገር
ፈጣሪህን አክብር ይላል የህግህ በር ።
(ሚካኤል.አ)
@getem
@getem
@getem
ምኞትን ያህል ነገር ተፈጥሮ ስትቸረኝ
በእጁ አበጃጅቶ የኳላትን እንስት ደጄ እያሳየኝ
አታመንዝር አለኝ!
.
እግዜሩ ነው የሚገርመኝ
በእሾህ በአሜኬላ ዓለሚቷን አጥሮ
አዳም ይብላ አለ በላቦቱ ግሮ።
እሺ የት እንስራ?
በዚም በዛም ያለው አለበት ደንቃራ
በቃ ልስረቅ ልንጠቅ
ቀን መሽቶ ቢያልፍልኝ...
እንዲህ አልል ነገር የርሱ ህግ አለብኝ።
.
እውነት!
እውነት!
እውነት!
እግዜሀር ነህ የምትገርመኝ
ድመት አርገህ ፈጥረህ ወተት አትንጠቀኝ
ነብር አርገህ ፈጥረህ ፍየል አትስረቀኝ
ስትለኝ...
እንደዚህ አትበለኝ...
ብዬም አልበሳጭ አልሳደብ ነገር
ፈጣሪህን አክብር ይላል የህግህ በር ።
(ሚካኤል.አ)
@getem
@getem
@getem
👍46❤28👎16😁5🔥4
#እግዜሩ ነህ የምትገርመኝ
ምኞትን ያህል ነገር ፣ ተፈጥሮ ስትቸረኝ
በእጅህ አበጃጅተህ የኳልካትን እንስት ደጄ እያሳየኝ
አታመንዝር አልከኝ!
.
እግዜሩ ነህ የምትገርመኝ
ምድሪቷ ታጥራብን ፣ በእሾህ አሜኬላ
ወዙን ሲያዘንብ ነው ፣ አዳም የሚበላ።
እህስ እንዴት ይሁን?
ተመልከት መንገዱን…
በዚ’ም በዛ’ም ያለው ፣ አለበት ደንቃራ
በቃ ልስረቅ ልንጠቅ
ቀን መሽቶ ቢያልፍልኝ...
እንዲህ አልል ነገር ፣ እሳት ዲን አለብኝ።
.
እውነት!
እውነት!
እውነት!
እግዜሀር ነህ የምትገርመኝ
ድመት አርገህ ፈጥረህ “ወተት አትንጠቀኝ”
ነብር አርገህ ፈጥረህ “ፍየል አትስረቀኝ”
እያልከኝ ፣
እንደዚህ አትበለኝ...
ብዬም አልበሳጭ ፣ አላሸሙር ነገር
ፈጣሪህን አክብር ይላል የሕግህ በር ።
(ሚካኤል.አ)
@getem
@getem
@getem
ምኞትን ያህል ነገር ፣ ተፈጥሮ ስትቸረኝ
በእጅህ አበጃጅተህ የኳልካትን እንስት ደጄ እያሳየኝ
አታመንዝር አልከኝ!
.
እግዜሩ ነህ የምትገርመኝ
ምድሪቷ ታጥራብን ፣ በእሾህ አሜኬላ
ወዙን ሲያዘንብ ነው ፣ አዳም የሚበላ።
እህስ እንዴት ይሁን?
ተመልከት መንገዱን…
በዚ’ም በዛ’ም ያለው ፣ አለበት ደንቃራ
በቃ ልስረቅ ልንጠቅ
ቀን መሽቶ ቢያልፍልኝ...
እንዲህ አልል ነገር ፣ እሳት ዲን አለብኝ።
.
እውነት!
እውነት!
እውነት!
እግዜሀር ነህ የምትገርመኝ
ድመት አርገህ ፈጥረህ “ወተት አትንጠቀኝ”
ነብር አርገህ ፈጥረህ “ፍየል አትስረቀኝ”
እያልከኝ ፣
እንደዚህ አትበለኝ...
ብዬም አልበሳጭ ፣ አላሸሙር ነገር
ፈጣሪህን አክብር ይላል የሕግህ በር ።
(ሚካኤል.አ)
@getem
@getem
@getem
❤35👍25😁10😱3👎2