#ውሉድ ወወላድ*
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም ! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ ! ምግባሩ ካለየ ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መሆን ክብር በከንቱ አይሰጥም !
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም !
እፍኝትን እይዋት . . .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣ በፍትወት መቃጠል ።
አንበሳም ደቦሉን . . .
በጊዜው ካልቀጣ ንግስናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል ።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ ፣
ካልተነፃፀረ ፤
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ ።
#የሞት ጥቁር ወተት
#ተስፋሁን ከበደ
@getem
@getem
@beckyalexander
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም ! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ ! ምግባሩ ካለየ ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መሆን ክብር በከንቱ አይሰጥም !
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም !
እፍኝትን እይዋት . . .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣ በፍትወት መቃጠል ።
አንበሳም ደቦሉን . . .
በጊዜው ካልቀጣ ንግስናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል ።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ ፣
ካልተነፃፀረ ፤
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ ።
#የሞት ጥቁር ወተት
#ተስፋሁን ከበደ
@getem
@getem
@beckyalexander
👍2
የፈጣሪ_ልሳን
እጆቼን ዘርግቼ........
ልጸልይ ልማልድ ከደጅኽ ተገኘኹ
አንጋጥጬ ሽቅብ በሐሳቤ ዋኘኹ
ተንበርክኬ ለምሕላ በግንባሬ ተደፍቼ
ቀና ማለት ተዘነጋኝ የቃል ጸሎት ረስቼ
ያ'ንደበትኸ ልሳን ከየት ተሠወረ?
ቃል ከምላሴ ላይ እንደምን ታወረ?
ዝም....
ዝም ዝም....... !
እንደው ዝም! ዝምታዬ ቀረ
ሰምተኸኛል አንተ
በዝምታ ልሳን ጸሎቴ ሰመረ።
ገጣሚ #ተስፋሁን_ከበደ
@getem
@getem
@paappii
እጆቼን ዘርግቼ........
ልጸልይ ልማልድ ከደጅኽ ተገኘኹ
አንጋጥጬ ሽቅብ በሐሳቤ ዋኘኹ
ተንበርክኬ ለምሕላ በግንባሬ ተደፍቼ
ቀና ማለት ተዘነጋኝ የቃል ጸሎት ረስቼ
ያ'ንደበትኸ ልሳን ከየት ተሠወረ?
ቃል ከምላሴ ላይ እንደምን ታወረ?
ዝም....
ዝም ዝም....... !
እንደው ዝም! ዝምታዬ ቀረ
ሰምተኸኛል አንተ
በዝምታ ልሳን ጸሎቴ ሰመረ።
ገጣሚ #ተስፋሁን_ከበደ
@getem
@getem
@paappii
❤63👍11🔥3🤩1