ግጥም ብቻ 📘
67.3K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ያደረግሽኝ በዝቶ.... ልቤን ያሳረረው
ጩኸቴን እንዳፍን
ምኑን ቀባብቼ ምኑን ልሞሽረው??!

ወልውዬ ሰጥቼሽ አፈር ካለበሽው
ጤነኛውን ልቤን መርዝ ካቀመሽው
በምን አማርኛ ትህትናን ጠልፌ
እንደው እንዲቀልሽ እንዴት ልበል ፅፌ??!!

አንቺ ኮ አታፍሪም ከበደልሽ በላይ
በጥሩ አማርኛ ስምሽ ገኖ ቢታይ
እንዳ-ላ-ጠፋ እንዳ-ል-በደለ
በከንቱ ንፁህ ........ እንዳልገደለ
ስጠብቂ ሳይ
                   ...... ያመኛል ብትይ!!!!

ነበረኝ ጥሩ ቃል ላንቺ ያላነሰ
ከልብ የተቀዳ ስንቱን የቦነሰ
የገፋሽው ድሮ .... ቀለለብኝ ያልሽኝ
ነበር አማርኛ ንቀሽ ያልሰማሽኝ
ከቃሉ ያደረ ... ፍፁም የከበረ
ብሰጥሽ ንፁህ ልብ ....... ያኔ ተሰበረ !!
እንደሞኝ ቆጥረሽው የተግባሬን ነገር
ባልኩት መገኘቴ ላንቺ ቀልድ ነበር

ታዲያ.............
ተመልሰሽ ዛሬ
ለምን ትይኛለሽ ተነካብኝ ክብሬ
ያኔ
አቅቶኝ ስቀጣ እያየሽኝ መራቅ
እንዴት ይገርምሻል
ደስታዬ ሲያድንሽ ፡ ሲሆንብሽ ጭራቅ!



ig & tiktok @be_Olyon


       ✍️ Olyon
                       
           
              አስተያየት (@be_Olyon)



     @getem
                   @getem
                                  @getem
               
👍5920
ማያልፍ የመሰለኝ ዳምኖ ህይዎቴ
ባዘነብኩት እንባ ታጥቦ ማንነቴ
ግርዶሹ በርትቶ ነገየን ጋርዶብኝ
ፍፁም አንዳልጓጓ ህመም በርትቶብኝ
ዛሬ ነገ እያልኩኝ ሞቴን ሲጠባበቅ
ህመሜን ሳዳምጥ ስሜቶቼን ሳረቅ
.
.
.
         መኖር ማለት ስቃይ
         መኖር ምለት ህመም
         መኖር ማለት ጭንቀት
         መኖር ማለት ድካም....

ወደ ተስፋ መንደር እልፍ ጊዜ ባመራ
የ እድሌን ልሻማ ከ እኩዮቼ ጋራ
ብፈልግ... ብጠብቅ ድርሻ የለኝ ሁኖ
ጠብታ እንኳን ሳይቀር ከ እኔነቴ ተኖ
ፀሐይ የለኝ ሁና ሕይዎቴ ዳምኖ
.
.
.
       ትላንት በመኖሬ ተስፋ እንኳን ሳይኖረኝ
       ምንም ያህል ባዝን የሚያልፍ ባይመስለኝ
       ቀን እየቆጠረ ቀን እየጨመረ
       የደመናው ጥቁረት መጠኑ ቀንሶ
       የስቃይ ዉርጅብኝ ከነበረው አንሶ
       ከ ሕይወቴ ጠፋ ቀስ በቀስ ጨርሶ...
.
.
.
የ ፀሐይ ዉበቷ
የፀሐይ ድምቀቷ
የዉበት ፍካቷ
ዛሬ ላይ ብሸፈን
ደመናው ሲገፈፍ ወደጎን ሲበተን....
.
.
.
       ህመም ብርድ ሁኖ ያገረጣው ትናንት
       ተንፏቆ እየዳሀ ዛሬን በመጠጋት
       አንድ ቀን ልጨምር ብዬ በመኖሬ
       ተስፋ ፀሐይ ሁኖ ከች አለልኝ ዛሬ!!
           
           📆ሚያዚያ 25 - 2016
                ዘይድ ሁሴን

@getem
@getem
@paappii
54👍47🔥3
በጥራት የተዘጋጀ   መሳያ ሸራ ይዘዙ
የዋጋ ለውጥ
20 x 20 cm ,,,200 ብር
25x25 cm. ..200 ብር
20*40cm.....300 ብር
30 x30  cm ....300 ብር
30*40cm ...300
30*60....350
40*80...500
40x 50 cm....400 ብር
40 x60 cm... 400 ብር
50 x60 cm....450 ብር
50 x70cm....450 ብር
60*80cm...550 ብር
100*60cm..750ብር
80*100...800 ብር
100*100cm  850ብር
80*120...900ብር
100*120....1100 ብር

Canvasochin እና የ ስዕል ማስዋቢያ frame ይዘዙን በ ጥራት እንሰራለን
ለበለጠ መረጃ በ 0934039346 ይደውሉልን
👍167
የቀረው

ቤት ሙሉ ዕቃ
ግቢ ሙሉ አበባ
ጠፈር ሙሉ ሰማይ
ተስፋን የተቀባ

ወንበሩ ሁሉ ሰው
ጠረጴዛው ምግብ
ቀኑ ሁሉ ድግስ
ሆድ ሁሉ ሲጠግብ

አፍ ሁሉ ፈገግታ
እጅም የሰላምታ
በጊዜ እሽሩሩ
ስቃይም ሲረታ

በምቾቱ ጭጋግ
ሲሸፈን ያለፈው
እንዳይከፈት አርጎ
ልቤን የቆለፈው

አንድ አለ
የረጋ ባዶነት
የቢሆን ጥያቄ
የምናልባት ውጋት!

ቅር ቅር የሚያሰኝ
በጩኸቶች ሁሉ ፤ ዝምታን ሚቀኝ
ከሳቅ የሚያርቀኝ
ያፈራሁት ሁሉ ፤ አልዋጥ እንዲለኝ
ምን ይሆን ያነቀኝ?

አምናን ለፍርሀት ፤ ትላንትን ለኩራት
የገበርኳትን ልብ ፤ ብለምን ብጠራት
ካስቀመጥኳት የለች ፤ ብፈልግ አጣኋት
እሷ ትሆን... መሰለኝ
ያዳፈንኩት እሳት ፤ እኔን አበሰለኝ
ሰም እና ወርቁንም ፤ ለይቶ አስተማረኝ።

አሁን የተረፈኝ...
በሞቀው ድባብ ውስጥ
ቀዝቀዝ ያለ እውነት
በፈካው ቀንም ላይ
ድብዝዝ ያለ እምነት

ድብዝዝ ያለ ተስፋ
በር በር እያየ አርቆ የጠፋ
በመጣው ስው ብዛት እጥፍ የተከፋ

ኮቴዋን የለየ እሷን የፈለጋት
የረጋ ባዶነት
የቢሆን ጥያቄ
የምናልባት ውጋት!!!



✍🏽✍🏽✍🏽... E.Z(@EZpoemandfiction)

@getem
@getem
@getem
👍4335🔥1
አባቶች እናቶች
በፍቅር ተጋግዘው ፣ ያቆሙልን እውነት
በዘመን ጠልሽቶ...
ለእኛ ለልጆች ፣ ይመስለናል ተረት፡፡
።።።።።።
የኛ ትልቅ ችግር ፣ የኛ ትልቅ ህመም
"ተረት ተረት"ሲባል
መሰረት ሳንይዝ
"የመሰረት" ብሎ ፣" እሺ" እያሉ ማዝገም፡፡
።።።።።።፣
ተረት ተረት
"የመሰረት"
አንድ ሀገር ነበረች
"እሺ"
እምነትን ከፍቅር ፣ ገምዳ ያስተማረች፡፡
"እሺ"
አናም በዚች ሀገር...
ሙስሊሞች በእምነት ፣ መስጅድ ሲገነቡ
ክርስቲያኖች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ምሶሶ ሲያቀርቡ፡፡
"እሺ"
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም በዚች ሀገር...
ክርስቲያኖች በምነት ፣ ቤተስኪያን ሲያንፁ
ሙስሊሞች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ጉልላት ሲቀርፁ፡፡
"እሺ"
እናም በዚ መልኩ ፣ ሲኖሩ ሰኖሩ
እንደተዋደዱ እንደተፋቀሩ
እንደተጋገዙ እንደተባበሩ
መሰረት እንድናይ...
አንዋር ከራጉኤል ፣ ተጎራብተው ቀሩ
"እሺ"
"እሺ" ማለት ጥሩ
መሰረት ሳይዙ ...
የመሰረት ብሎ ፣ መኖር ነው ችግሩ!!!
።።።።።

By Belay Bekele Weya

@getem
@getem
@paappii
👍4719👎2🔥2
( እግዚአብሔር ያመርራል .. )
=====================

ትዝ ይልሻል አይደል
ያኔ ሌላ ለምደሽ ስትሄጂ ትተሽኝ
በምጸት በውሸት ቃል
" ከኔ የተሻለች ሴት ይገባሀል " ያልሽኝ
ባይዋጥልኝም በዓለም የማፈቅረው
ካንቺ ሌላ እንዳለ ....
ውስጤን እየበላኝ አንጀቴ እያረረ
በየዋህ ልቡና .. መልሴ ' አሜን ' ነበረ

ታዲያ ዛሬ ሳያት ያሁኗ ወዳጄን
ቤቴን የምትሞላ ምታሞቀው ደጄን
ፍቅሯ ህሊናዬን ነፍሴን ሲያስደንቃት
ውልብ ይልብኛል የዛኔው ምርቃት

ለካ እምነት እስካለ ሁሉ ይቆጠራል
ሰው ገፍቶ የናቀውን እግዚአብሔር ያከብራል
ለካ ከሀሰት እጥፍ ... እውነት ሺ ያበራል
ሰው የቀለደውን እግዚአብሔር ያመርራል !!

By @kiyorna

@getem
@getem
@paappii
53👍22🔥3👎1
3👍3
.............😇ህልሟ😇.............

ከደስታ በር ቆሜ
ወደእኔ መጣች ፤ ሳታልፈኝ አስቆምኳት
ጠየኳት

ምን ትፈልጊያለሽ ፤ ህልምሽን ንገሪኝ?
ትንሽ አመንትታ
መኪና ቤት አለች ፤ የቀደመን አይታ

ከዛም አለፈችኝ
ስትሄድ ሸኘኋት ፤ ዞራም አላየችኝ።

ከደስታ በር ቆሜ
ወደእኔ መጣች ፤ ሳታልፈኝ አስቆምኳት
ጠየኳት

ምን ትፈልጊያለሽ ፤ ህልምሽን ንገሪኝ
ትንሽ አመንትታ
ትዳር ከዛም ልጆች .... የቀደመን አይታ

ከዛም አለፈችኝ
ስትሄድ ሸኘኋት ፤ ዞራም አላየችኝ

ከደስታ በር ቆሜ
ወደእኔ መጣች

ደክማለች
መሮጡ ታክቷታል
ያፍላነት እሳቷ ፤ በጊዜ ተረቷል

ሳታልፈኝ አስቆምኳት
ጠየኳት

ምን ትፈልጊያለሽ
ህልምሽን ንገሪኝ?

ዝም አለችኝ ላፍታ ፤ አየችኝ በአንኩሮ
ከሳሁ ጠቆርኩ ፤ ልበን ደርሻለሁ ፤ የለሁም ዘንድሮ
የነፍሷ ጥሪ ፤ የመንፈሷ ለቅሶ ... ነበርኩ
ስጋዋ የከዳኝ ፤ በስሜት የታሰርኩ

አነባች ለአፍታ
በሀዘኗ እውነት ፤ እውር አይኗ በራ
ይሉኝታም ተረታ

ለአፍታ ህይወቷ ፤ ትላንት ለኖረችው
ሞተ ገደለችው
አነባች አዘነች ፤ ከዛም ቀበረችው።
ዳግም ተወለደች
እኔን ያዘችና ፤ አይኖቿን ጨፈነች።


በህይወት ሸራዋ ፤ እጇ ላይ ታች አለ
ልቧም ደም አነባ ፤ አለም ተነከረ
ማንም አላያትም
ዳኝነት ይሉኝታም ፤ ተኝተው ነበረ

ጊዜዋም ሲያበቃ
አይኗን ገልጣ ፤ ፈገግ አለች
መጨረሻም ህልሟን ሳለች

እሱም ውብ ነበር!


✍🏽✍🏽✍🏽... E.Z(@EZpoemandfiction)

@getem
@getem
@getem
👍5410👎2
ተምታቶብኝ አይደል
ሺህ ጊዜ ብመርጣት ... ሺህ ቦታ ልሰጣት
ረስቼ አይደል
የሷን አለመሙላት ...... ወዳጄ ነሽ ብላት
.............................. አቃለው ሲጎድላት!
መቼ ረስቼ
ምን ብታስቀይም ብዙ ብታስለፋኝ
እሷን ትቶ መሄድ ለኔ መቼ ጠፋኝ
.................... አቀለው ሲከፋኝ!
እንደሱ አይደለም
ብዙ ደጋግሜ ደስታዬን ልለቅም
ስንቴ ብርቃትም
ሲከፋኝ ነው እንጂ ሲደላኝ አላቅም!!
አይቻለውና
የምችለው መስሎኝ
ናፍቆቷ ሲቀጣኝ ምኞቴ ነጥሎኝ
ታምሚያለውና
ህይወቴ ሲጨልም ተስፋ ሲሄድ ጥሎኝ
............................... እረ ምኑን ቀሎኝ!!!
እድሌ ናት በቃ
ሁሌ ምታፈላኝ .... የልቤ ሞቅታ
ሁሌ የምታመኝ የነብሴ ስቅታ
ብትደላም ባትደላም
የኔ ገፅ ብቻውን ያለ'ሷ አይሞላም!
              

   
Follow my IG & Tiktok @be_Olyon

       ✍️ Olyon
                       
           
              አስተያየት (@be_Olyon)


     @getem
                   @getem
                                  @getem
41👍24🔥7🤩1
የሞተ ፍቅር

ፍቅር ሲፈርስ
ከኮዳው ሲፈስ
ከጆንያ ሲበተን
ከገንዳው ላይ ሲተን
ፍቅርን አዬሁት
እንዳልተ መኘሁት


ውሀ እንዳጣ ተክል  መንምኖ
እንደ ሀምሌ ሰማይ  ዳምኖ
እንደ ወራጂ ውሀ ድፍርስ ብሎ
እንዳልመጣ ሁሉ  ተንበልብሎ
ጠራርጎ ሲያልፍ እሱም ያልቃል
ከታተመበት  ልብ ላይ ይፋቃል

ነፍስ የዘራው ነፍስ ሲያጣ
እያወዛ  ያደመቀው  ሲገረጣ
እርቆ ሊሄድ  ለሞት ዳና ያቃጥራል
ስንገድለው  ለነፍስ ውጭ ያጣጥራል
እንደዘበት ትዝታ ሆኖ ይቀራል

By kerim

@getem
@getem
@paappii
👍3121👎1
ከከፍታ የሚልቅ ዝቅታ
==============

የሰማይ ዳስ ተሰርቶላት፣
ማማለዱ ሆኖ ግብሯ
እመቤቲት የሁሉ እናት፣
የባሪያ ነው ንግግሯ
ሳይቸግራት ፈውስ መሆን፣
ፍምን ያህል አድሮ ሆዷ
በማነሷ ነው ማርያም፣
ከፍ ካሉት መወደዷ


ዘማርቆስ
28/07/2016
By GIZE

@getem
@getem
@getem
100👍36👎4🔥3😱1
ገንፎ

ሀገሬስ ገንፎ ናት
በስልጣን ማንኪያቸው የሚቆራርሷት
ቂቤ ወሬያቸውን በርበሬ ስራቸው
ጨመር አርገውባት
እሷ ያዝኩት ስትል
የስጧትን ሁሉ አጣቅሰው አላውሰው
በዛ ስልጣን ማንኪያ በህብረት አብረው
ያውም ክብ ሰርተው
እንደ ጉድ ሚበሏት የሚጎራረሷት
ሀገሬ ለእነርሱ ገንፎ ብቻ እኮ ናት
@topazionnn
@getem
@getem
👍72😢244🔥2
ያውቃል የልቦናን መልስ አለው በጊዜው
አያደርግ ይመስል ለምን ነው ትካዜው?
በእኛ ጊዜ ላይሆን የፈጣሪ መልሱ
ባለበት እስኪሰጥ አምናቹ ታገሱ

በኪሩቤል አሰፋ @Ebuh_bhr

@getem
@getem
@paappii
78👍28🔥4🤩2
የአባይን ልጅ...

አባይ ተገድቦ
                  ሆኖ ከደጃፌ

ሠፊው ጣናም ሞልቶ
                    ሳለ ከበራፌ

አዋሽና ጊቤ
               ተከዜና ባሮ

ማግኘት እየቻልኩኝ
                    ከሀገሬ ጋሮ

በዚህ ከባድ ኑሮ
                 ሁሉን ነገር ትቼ

እኔ በጥም ብዛት
                አለውኝ ገርጥቼ

ከድፍን ሀገሩ አንዲት ውሀ አጣጭ
               ለራሴ አጥቼ::

📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝

       ✍️ @BEGITIMENAWGA

@getem
@getem
@getem
👍5038😁34🤩3
Audio
👆👆👆 አሪፍ ግጥም በአሪፍ አቀራረብ ተጋበዙልኝ::    
        
               በቃሉ ሹምዬ
                🎙 ያኔት
Editor: @begitimenawga


🤰መልካም የእናቶች ቀን

📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝

@getem
@getem
@getem
31👍26🔥2😢1
❤️አልጎደልኩም❤️

አንዲት ትንሽ አጥንት
ከጎኔ አንስቶ

አምላክ ህይወት ሰጠኝ
አንቺን ለኔ ሰርቶ

ምንም ብባዝንም
ለጎደለው ጎኔ

ሙሉ አርገሺኛል
ስትመጪ ወደኔ።

📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝

       ✍️ @BEGITIMENAWGA

@getem
@getem
@getem
46👍34🔥4
እንባማ ወንዝ ነው ያልፋል እንደዘበት
ቢያብሱት ይደርቃል አፅናኝ በሞላበት
ክፉ የውስጥ ነው የማይደርቅ በሽታ
እንባ የማይመልሰው ልብ ያዘነ ለታ!


   
Follow my IG & Tiktok @be_Olyon

       ✍️ Olyon
                       
           
              አስተያየት (@be_Olyon)


     @getem
                   @getem
                                  @getem
👍6129😢6🔥3🎉3
🌹🌹በእሾህ ተከበሽ🌹🌹

ፅገሬዳ አበቦች በድንገት ሳያቸው
             ትዝ ትዪኛለሽ

እሾህሽ ብዙ ነው የግሉ ሊያረግሽ
            ከልብ ለተመኘሽ

እኔ ግን ከርታታው ጉልበተኛ ባልሆን
            ገንዘብ ባይኖር ኪሴ

እውነተኛ ፍቅሬን ተጠቀምኩኝና
              አረኩሽ የራሴ።

📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝

       ✍️ @BEGITIMENAWGA

@getem
@getem
@getem
48👍35🔥4🎉2👎1
🤔ቅኔ የሆንሽብኝ🙄

ለመጀመሪያ ቀን እንዳየሁሽ እኔ

ሁሉነገር ነበር የሆነብኝ ቅኔ።

ፊት ለፊት ያለውን ሰሙን እያየሁኝ

ሀዘን ሞላው ውስጤን መተከዝ ገባሁኝ።

ሆኖም ልቤን ስከፍት ጠፋና ሀዘኔ

ወርቅ እንዳገኘሁኝ አየሁት በአይኔ።

📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝

       ✍️ @BEGITIMENAWGA

@getem
@getem
@getem
👍5015