ግጥም ብቻ 📘
67.6K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
#ሁለት_ገፅታ

አይዳንድ ጊዜ : ሰዉ ከራስ ሲስማማ፣
ሲሄድ ሲራመድ : በሀሳብ ማማ፤
አይጣል ነዉ ነገሩ፣
አይፈታ ሚስጢሩ።

ሰዉ . . . .
ከራስ ተስማምቶ : ሲመቸዉ ጊዜያቱ፣
ረጥቦ ሲለመልም : ዉስጠት አንጀቱ፤

ፈጣሪን አይሰማ : ከራሱ ሲጣላ፣
ራሱን ተመክቶ : አያገኝ ከለላ።

ሀሴት ሲጎናፀፍ፣
በቀሽም ሀሳብ : ከጎን ሲደጋገፍ፤

ያገኘ ሲመስለዉ : ኪሱ ሲሞላ፣
ጠግቦ ስለዋለ : ሲሞላ(ሞ) በተድላ፤

ሚስጢር ነዉ ነገሩ፣
አይጣል ነዉ ሚስጢሩ።

ደግሞም . . . . .
ሲከፋዉ . . .ተድላ ሲከዳዉ፣
ሆድ ሲብሰዉ : ባዶነት ሲሰማዉ(ሰ)፤

ከራሱ አይስማማ፣
ከቶ አይራመድ : በሀሳብ ማማ።

. . . . .
ደግሞም ደግሞም፣
ሰዉ ከራስ ተጣልቶና ከርሞም፤

ሲናከስ ከሀሳቡ፣
ሲኮፈስ ከልቡ፤

ሲራቆት ሲናቆር፣
ሲፋጅ ሲሸናቆር፤

ሲከፋዉ በሆዱ ሲከዳ፣
የልቅሶ እንባ ከልቡ ሲቀዳ፤

ማልቀስ፣
ከሁሉ መናከስ፣
ከህይወት መፋለስ፤

ስራዉ ሆኖ በየጊዜው፣
ፈጣሪን ያማራል: ሆዱ ሲጎለዉ።

ደግሞም . . . . .
ከራስ ተስማምቶ : ሲመቸዉ ጊዜያቱ፣
ረጥቦ ሲለመልም : ዉስጠት አንጀቱ፤

ይኖራል ፈጣሪን ረስቶ፣
ነፍስ እያለዉ ሞቶ።

ይኖራል ረስቶ አስራቱን፣
ደሀዉን መቀለቡን፣
እጅ መዘርጋቱን።

ይኖራል ረስቶ : የእዉነትን አምላክ፣
ያቺን የፈጣሪ እናት : ያቺን ወላዲተ አምላክ።


እንግዲህ . . . .
የዚህ አለም ኑሮ : እንዲህ ነዉ በየአይነት፣
ሲያጡ ፈጣሪን መፈለግ : ሳይነጋ ለማግኘት።
ሲያገኙም አምላክን መሸሽ : ሲመሽ ላለመገኘት።

በቃ ይህ አለም : እንዲህ ነዉ ሀቁ : የሞላዉ ልዩነት፣
ማግኘት ማጣት ሰፍቶ : ጠፍቶ አንድነት፣
ያገኙትን ማጣት : ያጡትን መግኘት።

18 / 10 / 2010

@getem
@getem
@getem
👍1